ንዑስ ምድቦች

የሓዲሦች ዝርዝር

1. አንዲት ሴት ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) በተሳተፉበት አንድ ጦርነት ላይ ተገድላ ተገኘች። የአላህ መልክተኛም (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ሴትና ህፃናትን መግደልን አወገዙ።
عربي እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ
2. ከስለት ከለከሉ። እንዲህም አሉ "እርሱ መልካምን ይዞ አይመጣም። በስለት የሚገኘው ትርፍ ስስታም ተገዶ ማውጣቱ ብቻ ነው።
عربي እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ
3. እኔ ወላሂ አላህ ከሻ በአንድ ጉዳይ ከማልኩ በኋላ ተቃራኒው የተሻለ ሆኖ ከታየኝ የተሻለውን ፈፅሜ ለመሀላዬ ማካካሻ አደርጋለሁ እንጂ ከዚህ ውጪ ሌላ አላደርግም።" አሉን። - 2 ملاحظة
عربي እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ
4. በዱንያ ሐር የለበሰ ሰው በመጪው ዓለም አይለብሰውም።
عربي እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ
5. ትልቁ ጂሃድ የሚባለው ግፈኛ ባለስልጣን ዘንድ ፍትሀዊ ንግግርን መናገር ነው።
عربي እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ
6. ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ሌሊት የተነሱ ጊዜ አፋቸውን በመፋቂያ ይፍቁ ነበር።
عربي እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ
7. አንድ ሰውዬ ነቢዩን (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ስለ ትንሳኤ እለት ጠየቃቸው። "ትንሳኤ መቼ ነው?" አላቸው። እርሳቸውም "ለርሷ ምን አዘጋጅተሀል?" አሉት።
عربي እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ
8. ሰውዬው በጓደኛው ሃይማኖት ላይ ነው። አንዳችሁ የሚጎዳኘውን ሰው ይመልከት።
عربي እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ
9. የአላህ መልክተኛ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) "ያ ሙቀሊበል ቁሉብ ሠቢት ቀልቢ ዐላ ዲኒክ" (አንተ ልቦናን ገለባባጭ የሆንክ ጌታ ሆይ! ልቤን በሃይማኖትህ ላይ አፅናት) ማለትን ያበዙ ነበር።
عربي እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ
10. ውሻ ከአንዳችሁ እቃ የጠጣ ጊዜ (እቃውን) ሰባት ጊዜ ይጠበው።
عربي እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ
11. ላኢላሀ ኢለሏህ በቀረበው አደጋ ለዐረቦች ወዮላቸው! ዛሬ የየእጁጅና መእጁጅ ግድብ የዚህን ያህል ተከፍቷል።
عربي እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ
12. ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ከክፍሏ ከማትወጣ ልጃገረድ የበለጠ አይነአፋር ነበሩ። አንዳች የሚጠሉትን ነገር የተመለከቱ ጊዜ ፊታቸው ላይ ነበር የምናውቀው።
عربي እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ
13. የእውነት ሰማእትነትን እንዲሰጠው አላህን የጠየቀ ሰው ፍራሹ ላይ ቢሞት እንኳ አላህ የሰማእታትን ደረጃ ያደርሰዋል።
عربي እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ
14. አማኝ የሆነ ወንድና ሴት በርሱ ላይ ምንም ወንጀል የሌለበት ሆኖ አላህን እስኪገናኝ ድረስ በነፍሱ፣ በልጁና በገንዘቡ ላይ መከራ ከመከሰት አይወገድም።
عربي እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ
15. ጌታ ወደ ባሪያ እጅግ ቅርብ የሚሆነው በመጨረሻው የሌሊቱ አጋማሽ ነው።
عربي እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ
16. የትንሳኤ ቀን አንድ ሰውዬ ተይዞ ይመጣና እሳት ውስጥ ይጣላል። የሆዱ አንጀትም ይዘረገፋል። አህያ በወፍጮው እንደሚሽከረከረውም የተዘረገፈውን አንጀት ይዞ ይሽከረከራል።
عربي እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ
17. ይህ ከሰባ አመት ጀምሮ እሳት ውስጥ የተወረወረ ድንጋይ ነው። እርሱም እሳት ውስጥ ወደ ጥልቀቷ መጨረሻ ዛሬ እስኪደርስ ድረስ እየተምዘገዘገ ነበር።" አሉ።
عربي እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ
18. በአላህ መንገድ የሚዘምትን ያሰናዳ ሰው በርግጥም ዘምቷል። በአላህ መንገድ ለዘመተ ሰው (ቤተሰብ) በመልካም ትብብሩ የተተካ በርግጥም ዘምቷል።
عربي እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ
19. አላህ ከኔ በፊት በነበሩት ህዝቦች ውስጥ የላከው እያንዳንዱ ነቢይ ለርሱ ከህዝቦቹ መካከል ሱናውን (ፈለጉን) የሚይዙና በትእዛዙ የሚመሩ ሐዋርያትና ባልደረቦች አሉት።
عربي እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ
20. ከኔ በፊት አንድም አካል ያልተሰጠው አምስት ነገሮችን ለኔ ተሰጥተውኛል።
عربي እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ
21. ከየሁሉም ሶላት መጠናቀቂያ ላይ 'አልላሁመ አዒንኒ ዓላ ዚክሪከ፣ ወሹክሪከ፣ ወሑስኒ ዒባደቲክ' ማለትን እንዳትተው አደራ እልሃለሁ።" አሉኝ።» ትርጉሙም (አላህ ሆይ! አንተን በማውሳት፣ በማመስገንና አምልኮህን በማሳመር ላይ አግዘኝ።)
عربي እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ
22. አላህ እንዲህ ብሏል: ‹ሁሉም የአደም ልጅ ስራ ለርሱ ነው ፆም ሲቀር፤ ፆም ለኔ ነው። በርሱ የምመነዳውም እኔው ነኝ። - 10 ملاحظة
عربي እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ
23. አንዳችሁ ወንድሙን ያገኘ ጊዜ በርሱ ላይ ሰላምታን ያቅርብ! በመካከላቸው ዛፍ ወይም ግድግዳ ወይም ድንጋይ ከጋረዳቸው ከዚያም ድጋሚ ቢያገኘው በድጋሚ በርሱ ላይ ሰላምታን ያቅርብ።
عربي እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ
24. አንዳችሁ የተኛ ጊዜ በማጅራቱ ላይ ሸይጧን ሶስት ቋጠሮ ይቋጥራል። በየሁሉም ቋጠሮ ላይም ረጅም ሌሊት አለና ተኛ! እያለ ይመታል።
عربي እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ
25. እኔ ወደ ሰማይ ባረግኩበት ምሽት ኢብራሂምን አገኘኋቸው። እንዲህም አሉኝ ‹ሙሐመድ ሆይ! ለኡመትህ ከኔ የሆነን ሰላምታን አቅርብ! ጀነት ምርጥ አፈርና ጣፋጭ ውሃ እንዳላት
عربي እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ
26. በርግጥም ስለ ትልቅ ጉዳይ ነው የጠየቅከኝ፤ ጉዳዩ አላህ በርሱ ላይ ላቀለለለት ሰው ቀላል ነው።
عربي እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ
27. እናንተ ሰዎች ሆይ! አላህ መልካም ነው። ከመልካም በቀርም አይቀበልም። አላህ መልክተኞችን ባዘዘው ነገር አማኞችንም አዟል። - 2 ملاحظة
عربي እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ
28. ፍፁም ወዳጄ የሆኑት ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና ሶስት ነገሮች ላይ አደራ ብለውኛል። ከሁሉም ወር ሶስት ቀናት በመጾምን፣ የዱሓን ሁለት ረከዓ በመስገድንና ከመተኛቴ በፊት ዊትር መስገድን አደራ ብለውኛል።
عربي እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ
29. ጨረቃን ባያችሁ ጊዜ ፁሙ! ባያችሁት ጊዜ ፆም ፍቱ! ከተጋረደባችሁ ደሞ ልኩን ገምቱለት።
عربي እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ
30. ሰዎች ከቀደምት ነቢያት ካገኟቸው ቃላት መካከል ካላፈርክ የፈለግከውን ስራ! የሚለው አንዱ ነው።
عربي እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ
31. ‹የሚያጠራጥርህን ነገር ተውና ወደ ማያጠራጥርህ ሂድ! እውነት እርጋታን የተላበሰ ነው። ውሸት ደሞ ጥርጣሬን የተላበሰ ነው።›
عربي እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ
32. በዱንያ ውስጥ ልክ እንደ እንግዳ ወይም እንደ መንገድ አላፊ ሁን።
عربي እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ
33. ምላስህ አላህን በማውሳት ከመርጠብ አይወገድ።
عربي እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ
34. እንዳትገድለው! ከገደልከው እርሱ ከመግደልህ በፊት የነበርክበት ደረጃ ላይ ይሆንና አንተ ደሞ የተናገረውን ንግግር ከመናገሩ በፊት በነበረው ደረጃ ላይ ትሆናለህ።" አሉ።
عربي እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ
35. ነጭ ሽንኩርት ወይም ቀይ ሽንኩርት የበላ ሰው ከኛ ገለል ይበል ወይም ከመስጂዳችን ገለል ይበል። ቤቱም ይቀመጥ" አሉ።
عربي እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ
36. አላህና መልክተኛውን ለሚወድ፣ አላህም በእጁ ድልን የሚያጎናፅፈው ለሆነ አንድ ሰው ይህንን ባንዲራ እሰጣለሁኝ።
عربي እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ
37. መሪያችሁን ስሙ ታዘዙም! በነርሱ ላይ የተሸከሙት ግዴታ አለባቸው። በናንተም ላይ የተሸከማችሁት ግዴታ አለባችሁ።" አሉ።
عربي እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ
38. ሙስሊምን መስደብ አመፀኝነት ነው። መግደሉ ክህደት ነው።
عربي እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ
39. አይሁዶችንና ክርስቲያኖችን በሰላምታ አትጀምሯቸው። ከመካከላቸው አንዱን መንገድ ላይ ባገኛችሁ ጊዜም ወደ ጠባቡ መንገድ አጣብቡት።
عربي እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ
40. ጉንጩን የመታ፣ አንገትያውን የቀደደ፣ በድንቁርና ጥሪ የተጣራ ከኛ አይደለም።
عربي እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ
41. ከናንተ መካከል ለጁሙዓ ሶላት የመጣ ሰው ይታጠብ።
عربي እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ
42. ስስታም ማለት እርሱ ዘንድ ተወስቼ በኔ ላይ ሶላት ያላወረደ ነው። - 2 ملاحظة
عربي እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ
43. ማለዳ ላይ ወይም ከቀትር በኋላ ወደ መስጂድ የሄደ ሰው ማልዶ በሄደና ከቀትር በኋላ በሄደ ቁጥር አላህ ለርሱ ጀነት ውስጥ መስተንግዶ ያዘጋጅለታል።
عربي እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ
44. በአዛንና ኢቃም መካከል የሚባል ዱዓ አይመለስም (ተቀባይነቱ ጥርጥር የለውም)። - 2 ملاحظة
عربي እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ
45. አልላሁመ አስሊሕ ሊ ዲኒለዚ ሁወ ዒስመቱ አምሪ - 2 ملاحظة
عربي እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ
46. ረቢግፊርሊ ኸጢአቲ፣ ወጀህሊ፣ ወኢስራፊ ፊ አምሪ ኩሊህ፣ ወማ አንተ አዕለሙ ቢሂ ሚኒ፣ አላሁምመግፊርሊ ኸጧያየ፣ ወዓምዲ፣ ወጀህሊ፣ ወሀዝሊ ወኩሉ ዛሊከ ዒንዲ፤ አላሁመግፊርሊ ማ ቀደምቱ፣ ወማ አኸርቱ፣ ወማ አስረርቱ፣ ወማ አዕለንቱ፤ አንተል ሙቀዲሙ፣ ወአንተል ሙአኺሩ፣ ወአንተ ዐላ ኩሊ ሸይኢን ቀዲር" ትርጉሙም "ጌታዬ ሆይ! ወንጀሌን፣ አለማወቄን፣ በሁሉም ነገር ወሰን ማለፌን፣ አንተ ከኔ የበለጠ የምታውቀውንም ማረኝ። አላህ ሆይ! ወንጀሌን፣ ሆን ብዬ የሰራሁትን፣ አለማወቄን፣ ቀልዴን ማረኝ፤ ይህ ሁሉም ከኔው ነው። አላህ ሆይ! ያስቀደምኩትን፣ ያዘገየሁትን፣ የመሰጠርኩትን፣ ግልፅ ያወጣሁትን ወንጀል ማረኝ፤ አንተ አስቀዳሚ ነህ፣ አንተም የሚያዘገይ ነህ፣ አንተም በሁሉም ነገር ላይ ቻይ ነህ።" ማለት ነው።
عربي እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ
47. አላህ ሆይ! በዱንያም ሆነ በመጪው አለም ደህንነትን እጠይቅሃለሁ፤ - 2 ملاحظة
عربي እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ
48. አልላሁመ ኢኒ አስአሉከ ሚነል ኸይሪ ኩሊህ፣ ዓጂሊሂ ወአጂሊህ፣ ማ ዓሊምቱ ሚንሁ ወማለም አዕለም፣ ወአዑዙ ቢከ ሚነ ሸሪ ኩሊህ፣ ዓጂሊሂ ወአጂሊህ ማዓሊምቱ ሚንሁ ወማለም አዕለም።
عربي እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ
49. አላሁመ ኢኒ አዑዙ ቢከ ሚን ዘዋሊ ኒዕመቲክ፣ ወተሐውዉሊ ዓፊየቲክ፣ ወፉጃአቲ ኒቅመቲክ፣ ወጀሚዒ ሰኸጢክ"» ትርጉሙም "አላህ ሆይ! ፀጋህ ከመወገዱ፣ ለኔ የሰጠኸኝ ደህንነት ከመቀልበስ፣ ከድንገተኛ መከራህ፣ ከአጠቃላይ ቁጣህ በአንተ እጠበቃለሁ።" ማለት ነው።
عربي እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ
50. አላህ ሆይ! እኔ በእዳ ከመሸነፍ፣ በጠላት ከመሸነፍና የጠላቶች ደስታ ምንጭ ከመሆን ባንተ እጠበቃለሁ።
عربي እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ
51. አልላሁመ ቢከ አስበሕና ወቢከ አምሰይና ወቢከ ነሕያ ወቢከ ነሙቱ ወኢለይከ ኑሹር
عربي እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ
52. ሴቶች ጋር ከመግባት ተጠንቀቁ!" አንድ ከአንሷር የሆነ ሰውዬም "የአላህ መልክተኛ ሆይ! ስለባል ቅርብ ዘመዶች ንገሩኝ እስኪ?" አለ። እርሳቸውም "የባል ቅርብ ዘመድማ ሞት ነው።" አሉ። - 2 ملاحظة
عربي እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ
53. ‹ብር በወርቅ እጅ በእጅ ካልሆነ በቀር አራጣ ነው፤ ስንዴ በስንዴ መለዋወጥ እጅ በእጅ ካልሆነ በቀር አራጣ ነው፤ ገብስ በገብስ መለዋወጥ እጅ በእጅ ካልሆነ በቀር አራጣ ነው፤ ተምር በተምር መለዋወጥ እጅ በእጅ ካልሆነ በቀር አራጣ ነው።›
عربي እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ
54. 'አሏሁመ‐ህዲኒ ወሰዲድኒ' (ትርጉሙም: አላህ ሆይ ምራኝ፣ አስተካክለኝም።) በልና መመራትን ከአሏህ ስትጠይቅ መንገድን መመራትን አስታውስ። መስተካከልን ስትጠይቅ ደሞ የቀስት ኢላማውን የማግኘት ያህል መገጠምን አስታውስ።
عربي እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ
55. እጅህን የሚያምህ ሰውነት ላይ አድርግና ሶስት ጊዜ "ቢስሚላህ" በል። ሰባት ጊዜ ደግሞ "አዑዙ ቢላሂ ወቁድረቲሂ ሚንሸሪ ማአጂዱ ወኡሓዚሩ" በል።» አሉት።" ትርጉሙም "ከሚሰማኝ ህመምና ከምፈራው አደጋ ክፋት በአላህና በችሎታው እጠበቃለሁ።" ማለት ነው።
عربي እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ
56. ‹ሶስት ጊዜ 'ቢስሚላሂለዚ ላየዱሩ መዐስሚሂ ሸይኡን ፊልአርዲ ወላፊስሰማእ ወሁወስ'ሰሚዑል ዐሊም' (ትርጉሙም: በዚያ ከስሙ ጋር በምድርም ይሁን በሰማይ ምንም ነገር የማይጎዳ በሆነው እንዲሁም ሰሚና አዋቂ በሆነው አላህ ስም።) ያለ ሰው እስኪነጋ ድረስ ድንገተኛ መከራ አያገኘውም።
عربي እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ
57. ፀሐይ ከመውጣቷና ከመግባቷ በፊት የሰገደ አንድም ሰው እሳት አይገባም።
عربي እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ
58. አንድም በኔ ላይ ሰላምታን የሚያቀርብ የለም ለርሱ ሰላምታን እስክመልስ ድረስ አላህ ለኔ ነፍሴን የሚመልስልኝ ቢሆን እንጂ።
عربي እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ
59. በሰዎች ውስጥ ሁለት ነገሮች አሉ፤ ክህደት ናቸው። በዘር መተቸትና በሞተ ላይ ሙሾ ማውረድ ናቸው።
عربي እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ
60. የወርቅና የብር ባለቤት ሆኖ ሐቃቸውን የማይወጣ ሰው የትንሳኤ ቀን ለርሱ የእሳት ዝርግ ተዘርግቶለት በርሷ በጀሃነም እሳት ውስጥ ሳይቃጠል የሚቀር የለም። ጎኑም፣ ግንባሩና ጀርባውም የሚተኮስ መሆኑ አይቀርም። - 4 ملاحظة
عربي እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ
61. (ለጀነት ነዋሪዎች) አንድ ተጣሪ ይጣራና "ለናንተ ጤና አላችሁ መቼም አትታመሙም፤ ለናንተ ህይወት አላችሁ መቼም አትሞቱም፤ ለናንተ ወጣትነት አላችሁ መቼም አታረጁም፤ ለናንተ በፀጋ ውስጥ መጣቀም አላችሁ መቼም አትቸገሩም።
عربي እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ
62. የጀነት ሰዎች ጀነት የገቡ ጊዜ አላህ ተባረከ ወተዓላ እንዲህ ይላል "አንዳች ነገር እንድጨምርላችሁ ትፈልጋላችሁን?
عربي እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ
63. እርሱ ውሃው አፅጂ ነው፤ ውስጡ የሞተም ሐላል ነው።
عربي እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ
64. ውሃው ሁለት 'ቁለተይን' ከደረሰ ነጃሳን አይሸከምም።
عربي እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ
65. አንዳችሁ ከእንቅልፉ የነቃ ጊዜ ሶስት ጊዜ አፍንጫው ውስጥ ውሃ እየከተተ ያውጣ፤ ሸይጧን በአፍንጫው ውስጥ ያድራልና።
عربي እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ
66. አንዳችሁ ዉዱእ አድርጎ ኹፎቹን የለበሰ እንደሆነ እነርሱን እንደለበሰ ይስገድ። በነርሱም ላይ ያብስና ከዚያም ለጀናባ ካልሆነ በቀር ከፈለገ አያውልቃቸው።
عربي እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ
67. አንድ ሰው ሌላን ሰው በአመፀኝነትም ሆነ በከሃዲነት አያነውረውም ባለቤቱ እንደዚያ ካልሆነ ወደርሱ ብትመለስ እንጂ።
عربي እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ
68. ሸይጧን በጀዚረተል ዐረብ (በባህር የተከበበው የዐረብ ምድር) ውስጥ ሰጋጆች ያመልኩኛል የሚለውን ተስፋ ቆርጧል። ነገር ግን በሰጋጆች መካከል ማጣላትን (ተስፋ አልቆረጠም)።
عربي እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ
69. (በአማና) በአደራ የማለ ሰው ከኛ አይደለም።
عربي እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ
70. እናንተ የሴቶች ስብስቦች ሆይ! ምጽዋት ስጡ! እኔ አብዛኛው የእሳት ነዋሪዎች ሆናችሁ አይቻችኋለሁ።" ሴቶቹም "የአላህ መልክተኛ ሆይ! በምን ምክንያት?" አሉ። እርሳቸውም "እርግማን ታበዛላችሁ፤ አኗኗሪን ትክዳላችሁ። አይምሮና ዲናቸው የጎደለ ሆኖ፤ ቆራጥ የሆነን ወንድ ልጅ ልብ የሚወስድም እንደናንተ አልተመለከትኩም!" አሉ። - 2 ملاحظة
عربي እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ
71. አዛን በሚሰማ ጊዜ ‹አልላሁመ ረበ ሀዚሂ አድደዕወቲ አትታመቲ ወስሰላቲል ቃኢመህ አቲ ሙሐመደኒል ወሲለተ ወልፈዲለተ ወብዐሥሁ መቃመን መሕሙደኒለዚ ወዐድተህ› ያለ ሰው የትንሳኤ ቀን ምልጃዬ ትፀድቅለታለች።" ትርጉሙም "የዚህ የተሟላ ጥሪና የምትቆመው ሶላት ጌታ የሆንከው አላህ ሆይ! ለሙሐመድ ወሲላና ፈዲላን ስጣቸው፤ ቃል የገባህላቸውን ምስጉን ስፍራም ስጣቸው።" ማለት ነው።
عربي እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ
72. አንዳችሁ ትከሻዎቹ ላይ አንዳችም ነገር የሌለ ሆኖ በአንድ ልብስ ብቻ አይስገድ።
عربي እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ
73. ሱጁድ በወረድክ ጊዜ መዳፎችህን መሬት ላይ አኑር! ክንድህንም ከፍ አድርግ!
عربي እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ
74. ከነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና ጋር ሰገድኩኝ። ወደ ቀኛቸው "አስሰላሙ ዐለይኩም ወረሕመቱላሂ ወበረካቱህ" በማለት ያሰላምቱ ነበር። ወደ ግራቸው ዞረው ደሞ "አስሰላሙ ዐለይኩም ወረሕመቱላሂ" ይሉ ነበር።
عربي እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ
75. የአላህ መልክተኛ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና ለአቡበከርና ዑመር እንዲህ አሉ: "እነዚህ ሁለቱ ከነቢያትና መልክተኞች ውጪ ከመጀመሪያው እስከመጨረሻው ካሉ የጀነት ነዋሪ ጎልማሶች አለቆቹ ናቸው።
عربي እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ
76. ሐሰንና ሑሰይን የጀነት ነዋሪ ወጣቶች አለቆች ናቸው።
عربي እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ
77. ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና ከዝሁር በፊት አራት ረከዓና ከፈጅር በፊት ሁለት ረከዓ አይተዉም ነበር።
عربي እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ
78. ከዝሁር በፊት አራት ረከዓዎች ላይና ከዝሁር በኋላ አራት ረከዓዎች ላይ የተጠባበቀ ሰው አላህ እሳትን በርሱ ላይ እርም አድርጎለታል።
عربي እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ
79. የአላህ መልክተኛ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና በፈጅር ሁለት ረከዓዎች ላይ {ቁል ያ አዩሃል ካፊሩን} እና {ቁል ሁወሏሁ አሐድ}ን አነበቡ።
عربي እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ
80. የአላህ መልክተኛ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና አንድ ሰውዬ ከሰልፍ ኋላ ብቻውን ሲሰግድ ተመለከቱትና ሶላቱን እንዲደግመው አዘዙት።
عربي እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ
81. ከወሊዩዋ (አሳዳጊዋ) ፈቃድ ውጪ ያገባች ማንኛዋም ሴት ጋባቻዋ ውድቅ ነው። (ንግግራቸውን ሶስት ጊዜ ደጋግሙት) እርሷን ከተገናኘም በመንካቱ ምክንያት መህሯ የራሷ ነው። ወሊዮች ከተጨቃጨቁም ወሊይ ለሌለው ሰው የሙስሊሞች መሪ ወሊዩ ነው።
عربي እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ
82. ሚስቱን በመቀመጫዋ የተገናኛት ሰው የተረገመ ነው።
عربي እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ
83. አላህ ወንድን ልጅ ወይም ሴትን ልጅ በመቀመጫ የተገናኘን ሰው (በእዝነት) አይመለከተውም።
عربي እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ
84. የአላህ መልክተኛ ሆይ! ሚስታችን እኛ ላይ ያላት ሐቅ ምንድን ነው? አልኩኝ። እርሳቸውም "ስትበላ ልታበላት፤ የለበስክ ወይም የሰራህ ጊዜ ልታለብሳት፤ ፊቷን ላትመታ፤ ላታጥላላት፤ ከቤት ውጪ ባለ ቦታ ላታኮርፋት ነው።" በማለት መለሱልኝ።
عربي እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ
85. ለርሱ ሁለት ሚስቶች ኑረውት ወደ አንዳቸው የተዘነበለ የትንሳኤ ቀን ጎኑ የተንሻፈፈ ሆኖ ይመጣል።
عربي እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ
86. አጋርያንን በገንዘባችሁ፣ በነፍሳችሁና በምላሳችሁ ታገሉ።
عربي እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ
87. የሙስሊም ሽርጥ እስከ ባቱ ግማሽ ድረስ ነው። ከባቱ ግማሽና በቁርጭምጭሚቱ መሃል ቢሆንም ግን ችግር የለውም። ከቁርጭምጭሚት ዝቅ ያለ ከሆነ እርሱ እሳት ውስጥ ነው። ሽርጡን በኩራት የጎተተን ሰው አላህ ወደርሱ አይመለከትም።
عربي እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ