+ -

عن المِقدام بن معدي كرب رضي الله عنه عن النبي صلى الله عليه وسلم قال:
«إِذَا أَحَبَّ الرَّجُلُ أَخَاهُ فَلْيُخْبِرْهُ أَنَّهُ يُحِبُّهُ».

[صحيح] - [رواه أبو داود والترمذي والنسائي في السنن الكبرى وأحمد] - [سنن أبي داود: 5124]
المزيــد ...

ከሚቅዳም ቢን መዕዲከሪብ እንደተላለፈው ነቢዩ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን እንዲህ ብለዋል:
"አንድ ሰው ወንድሙን ከወደደው እንደሚወደው ይንገረው።"

[ሶሒሕ ነው።] - [አቡዳውድ፣ቲርሚዚ፣ ነሳኢ በሱነኑል ኩብራ ፣ አሕመድ ዘግበውታል።] - [ሱነን አቡዳውድ - 5124]

ትንታኔ

ነቢዩ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም በምእመናን መካከል መስተጋብራቸውን ከሚያጠናክሩና በመካከላቸውም ውዴታን ከሚያሰፍኑ ሰበቦች መካከል አንዱን ጠቀሱ። ይኸውም አንድ ሰው ወንድሙን የሚወደው ከሆነ እንደሚወደው ይንገረው አሉ።

ትርጉም: እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ ስፔንኛ ኢንዶኔዥያኛ ኡይጙራዊ ባንጋሊኛ ፈረንሳይኛ ቱርክኛ ሩስያኛ ቦስንያኛ ሲንሃላዊ ህንድኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ቬትናማዊ ታጋሎግ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ማላያላምኛ ቴልጉ ስዋሒልኛ ታሚልኛ ቦርምኛ ታይላንድኛ ጀርመንኛ ጃፓንኛ ቡሽትኛ አሳምኛ አልባንኛ السويدية الهولندية الغوجاراتية Kyrgyzisht النيبالية Jorubisht الليتوانية الدرية الصربية الصومالية الطاجيكية Kinjaruandisht الرومانية المجرية التشيكية Malagasisht ጣልያንኛ Oromisht Kannadisht Azerisht الأوزبكية الأوكرانية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. ለዓለማዊ ጥቅም ሳይሆን ጥርት ባለ መልኩ ለአላህ ብሎ መውደድ ያለውን ደረጃ፤
  2. መዋደዱና መግባባቱ እንዲጨምር ለአላህ ብለው የሚወዱትን እንደሚወዱት መንገር እንደሚበረታታ፤
  3. በምእመናን መካከል መዋደድ መስፋፋቱ ኢማናዊ የሆነውን ወንድማማችነት እንደሚያጠነክርና ማህበረሰቡንም ከመለያየትና ከመበታተን እንደሚታደግ፤