عن جابر رضي الله عنه أن رسول الله صلى الله عليه وسلم قال:
«رَحِمَ اللهُ رَجُلًا سَمْحًا إِذَا بَاعَ، وَإِذَا اشْتَرَى، وَإِذَا اقْتَضَى».
[صحيح] - [رواه البخاري]
المزيــد ...
ከጃቢር ረዲየሏሁ ዓንሁ እንደተላለፈው የአሏህ መልዕክተኛ ﷺ እንዲህ ብለዋል፡
"ሲሸጥም፣ ሲገዛም ይሁን ያበደረውን ሲያስመልስ ገር የሆነን ሰው አሏህ ይዘንለት።"
Sahih/Authentic. - [Al-Bukhari]
ነቢዩ ﷺ ሲሸጥ ለስላሳ፣ ቸርና ለጋስ ለሆነ ሁሉ የአሏህን እዝነት እንዲያገኝ ዱዓእ አደረጉለት፤ ይህም ዋጋውን በማናር ገዥን አያጨናንቅም፤ ይልቁን በጥሩ ስነምግባር የሚግባባ ነው። ሲገዛም ለስላሳ፣ ቸርና ለጋስ ስለሆነ እቃውን በማሳነስና በማጣጣል ዋጋውን አያራክስም። ያበደረውን እዳ ሲያስመልስም ለስላሳ፣ ቸርና ለጋስ ስለሆነ ገንዘቡ እጅግ ያስፈለገውን ድሀ አያካብድበትም፤ ይልቁንም በእዝነትና ርህራሄ ይጠይቃል፤ ለተጨናነቀም የጊዜ ፋታ ይሰጣል።