عن جابر رضي الله عنه أن رسول الله صلى الله عليه وسلم قال:
«رَحِمَ اللهُ رَجُلًا سَمْحًا إِذَا بَاعَ، وَإِذَا اشْتَرَى، وَإِذَا اقْتَضَى».

[صحيح] - [رواه البخاري] - [صحيح البخاري: 2076]
المزيــد ...

ከጃቢር ረዲየሏሁ ዐንሁ እንደተላለፈው የአሏህ መልዕክተኛ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና እንዲህ ብለዋል፡
"ሲሸጥም፣ ሲገዛም ይሁን ያበደረውን ሲያስመልስ ገር የሆነን ሰው አሏህ ይዘንለት።"

[ሶሒሕ ነው።] - [ቡኻሪ ዘግበውታል።] - [ሶሒሕ አልቡኻሪ - 2076]

ትንታኔ

ነቢዩ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና ሲሸጥ ለስላሳ፣ ቸርና ለጋስ ለሆነ ሁሉ የአሏህን እዝነት እንዲያገኝ ዱዓእ አደረጉለት፤ ይህም ዋጋውን በማናር ገዥን አያጨናንቅም፤ ይልቁን በመልካም ምግባር ይዋዋለዋል። ሲገዛም ለስላሳ፣ ቸርና ለጋስ ስለሆነ እቃውን በማሳነስና በማጣጣል ዋጋውን አያራክስም። ያበደረውን እዳ ሲያስመልስም ለስላሳ፣ ቸርና ለጋስ ስለሆነ ገንዘቡ እጅግ ያስፈለገውን ድሀ አያካብድበትም፤ ይልቁንም በእዝነትና ርህራሄ ይጠይቃል፤ ለተጨናነቀም የጊዜ ፋታ ይሰጣል።

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. በሰዎች መካከል ያለን መስተጋብር ማስተካከል ሸሪዓው ከሚፈልጋቸው ዋንኛ ተፈላጊ ጉዳዮች መካከል መሆኑን እንረዳለን።
  2. በሽያጭና በግዥም ይሁን በሌላም መስክ ከሰዎች ጋር ባለን መስተጋብር እጅግ ያማረውን ስነምግባር መላበስ የሚበረታታ መሆኑን እንረዳለን።
ትርጉሞችን ይመልከቱ
ቋንቋ: እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ ስፔንኛ ተጨማሪ (67)