+ -

عن عبد الله بن عمرو رضي الله عنهما قال: قال رسول الله صلى الله عليه وسلم:
«إِنَّ الْمُقْسِطِينَ عِنْدَ اللهِ عَلَى مَنَابِرَ مِنْ نُورٍ، عَنْ يَمِينِ الرَّحْمَنِ عَزَّ وَجَلَّ، وَكِلْتَا يَدَيْهِ يَمِينٌ، الَّذِينَ يَعْدِلُونَ فِي حُكْمِهِمْ وَأَهْلِيهِمْ وَمَا وَلُوا».

[صحيح] - [رواه مسلم] - [صحيح مسلم: 1827]
المزيــد ...

ከዐብደላህ ቢን ዐምር -አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸውና- እንደተላለፈው እንዲህ አለ፦ የአላህ መልክተኛ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም እንዲህ ብለዋል፦
"ፍትሃዊዎች (የትንሳኤ ቀን) አላህ ዘንድ በብርሃን በተሰራ ወንበር ላይ ከአርራሕማን ቀኝ በኩል ይሆናሉ። ሁለቱም የአላህ እጆች ቀኝ ናቸው። (ፍትሃዊ የሚባሉትም) እነዚያ በፍርዳቸው፣ በቤተሰቦቻቸውና በተሾሙበት ጉዳዮች ላይ ፍትህን የሚያሰፍኑ ናቸው።"

[ሶሒሕ ነው።] - [ሙስሊም ዘግበውታል።] - [ሶሒሕ ሙስሊም - 1827]

ትንታኔ

እነዚያ በአመራራቸውና በፍርዳቸው ስር ያሉ ሰዎችን እና በቤተሰቦቻቸው መካከል በፍትህና በእውነት የሚፈርዱ ሰዎች የትንሳኤ ቀን ለነሱ ክብር ይሆን ዘንድ ከፍ ባሉ ከብርሃን በተፈጠሩ ወንበሮች ላይ እንደሚቀመጡ ነቢዩ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ተናገሩ። እነዚህም ወንበሮች በአርራሕማን ቀኝ በኩል የሚገኙ ናቸው። ጥራት የተገባው አላህ ሁለቱም እጆቹ ቀኝ ናቸው።

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. የፍትህ ትሩፋቱና በሱ ላይ መበረታታቱን እንረዳለን።
  2. ፍትህ በሰዎች መካከል ያሉ ሁሉንም ፍርድና ኃላፊነትን የሚያካትት ጠቅላይ ቃል ነው። በሚስቶች፣ በልጆችና በሌሎችም መካከል ፍትህ ማስፈን ሳይቀር ፍትሃዊነት ውስጥ ይገባል።
  3. የትንሳኤ ቀን የፍትሃዊዎች ደረጃ መገለፁን እንረዳለን።
  4. ሁሉም በስራው ልክ ስለሚመነዳ የትንሳኤ ቀን የኢማን ባለቤቶች ደረጃ የሚበላለጥ መሆኑን እንረዳለን።
  5. በማነሳሳት የማስተማር ዘይቤ የሚማሩትን ሰዎች ትምህርቱን እንዲቀበሉ የሚያነሳሳ ከሆኑት የማስተማር ዘይቤዎች መካከል መሆኑን እንረዳለን።
ትርጉም: እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ ስፔንኛ ኢንዶኔዥያኛ ኡይጙራዊ ባንጋሊኛ ፈረንሳይኛ ቱርክኛ ሩስያኛ ቦስንያኛ ሲንሃላዊ ህንድኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ቬትናማዊ ታጋሎግ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ማላያላምኛ ቴልጉ ስዋሒልኛ ታሚልኛ ቦርምኛ ጀርመንኛ ጃፓንኛ ቡሽትኛ አሳምኛ አልባንኛ السويدية الهولندية الغوجاراتية Kyrgyzisht النيبالية Jorubisht الليتوانية الدرية الصربية الصومالية الطاجيكية Kinjaruandisht الرومانية المجرية التشيكية الموري Malagasisht الفولانية Oromisht Kannadisht الولوف البلغارية Azerisht اليونانية الأكانية الأوزبكية الأوكرانية الجورجية المقدونية الخميرية
ትርጉሞችን ይመልከቱ