عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ رَضيَ اللهُ عنه أَنَّ رَسُولَ اللهِ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ، قَالَ:
«أَحَبُّ الْبِلَادِ إِلَى اللهِ مَسَاجِدُهَا، وَأَبْغَضُ الْبِلَادِ إِلَى اللهِ أَسْوَاقُهَا».
[صحيح] - [رواه مسلم] - [صحيح مسلم: 671]
المزيــد ...
ከአቡ ሁረይራ -አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው የአላህ መልክተኛ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና - እንዲህ ብለዋል፦
"አላህ ዘንድ እጅግ ተወዳጁ ስፍራ መስጂዶች ናቸው። አላህ ዘንድ እጅግ የሚጠላው ስፍራ ገበያዎች ናቸው።"
[ሶሒሕ ነው።] - [ሙስሊም ዘግበውታል።] - [ሶሒሕ ሙስሊም - 671]
ነቢዩ -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- አላህ ዘንድ እጅግ ተወዳጁ ስፍራ መስጂዶች እንደሆኑ ተናገሩ። ይኸውም የአምልኮ ቤቶችና ምስረታቸውም አላህን በመፍራት ላይ ስለሆነ ነው። አላህ ዘንድ እጅግ የተጠላውም ስፍራ ገበያዎች እንደሆኑ ተናገሩ። ይኸውም በአብዛኛው ማታለል፣ መሸወድ፣ ወለድ፣ የውሸት መሃላ፣ ቃልን ማፍረስና አላህን ከማስታወስ ችላ የሚባልበት ስፍራ ስለሆነ ነው።