عن أبي موسى رضي الله عنه قال: قال رسول الله صلى الله عليه وسلم:
«إِنَّ اللهَ لَيُمْلِي لِلظَّالِمِ، حَتَّى إِذَا أَخَذَهُ لَمْ يُفْلِتْهُ» قَالَ: ثُمَّ قَرَأَ: «{وَكَذَلِكَ أَخْذُ رَبِّكَ إِذَا أَخَذَ الْقُرَى وَهِيَ ظَالِمَةٌ إِنَّ أَخْذَهُ أَلِيمٌ شَدِيدٌ}[هود: 102]»

[صحيح] - [متفق عليه]
المزيــد ...

ከአቡ ሙሳ -አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸውና- እንደተላለፈው እንዲህ አሉ: "የአላህ መልክተኛ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም እንዲህ ብለዋል:
'አላህ በዳይን ያዘገየዋል። የያዘው ጊዜ ግን አይለቀውም!'" አቡ ሙሳ እንዲህ አለ: "ቀጥለውም {የጌታህም ቅጣት የከተሞችን ሰዎች እነሱ በዳዮች ሲሆኑ በቀጣቸው ጊዜ እንደዚህ ነው። ቅጣቱ በእርግጥ አሳማሚ ብርቱ ነው።} [ሁድ: 102] የሚለውን አነበቡ።"

Sahih/Authentic. - [Al-Bukhari and Muslim]

ትንታኔ

ነቢዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም በወንጀል፣ በሽርክና ሰዎችን በመብታቸው በመበደል ላይ ከመዘውተር አስጠነቀቁ። ምክንያቱም አላህ በዳይን ያዘገየዋል፣ ያቆየዋል ፣ እድሜውንና ገንዘቡንም ያረዝምለታል። በቅጣትም አያቻኩለውም። ካልቶበተ ግፉ ስለበዛ ይይዘዋል አይለቀውምም አይተወውምም።
ቀጥለውም ነቢዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም {የጌታህም ቅጣት የከተሞችን ሰዎች እነሱ በዳዮች ሲሆኑ በቀጣቸው ጊዜ እንደዚህ ነው። ቅጣቱ በእርግጥ አሳማሚ ብርቱ ነው።} [ሁድ: 102] የሚለውን አነበቡ።

ትርጉም: እንግሊዝኛ ፈረንሳይኛ ስፔንኛ ቱርክኛ የኡርዱ ቋንቋ ኢንዶኔዥያኛ ቦስንያኛ ሩስያኛ ባንጋሊኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ታጋሎግ ህንድኛ ቬትናማዊ ሲንሃላዊ ኡይጙራዊ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ማላያላምኛ ቴልጉ ስዋሒልኛ ታሚልኛ ቦርምኛ ታይላንድኛ ጀርመንኛ ጃፓንኛ ቡሽትኛ አሳምኛ አልባንኛ السويدية الهولندية الغوجاراتية الدرية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. አስተዋይ የሆነ ሰው ወደ ተውበት መቻኮል ይገባዋል። በበደል ላይ የዘወተረ ጊዜ አላህ አዘናግቶ እንደሚይዘው መጠራጠር የለበትም።
  2. አላህ በዳዮችን ማዘግየቱና እነሱን በመቅጣት አለመቻኮሉ እነሱን ማዘናጊያና ካልቶበቱ ቅጣታቸውን ማነባበርያ ነው።
  3. ግፍ የአላህን ቅጣት ህዝቦች ላይ የሚያመጣ አንዱ ምክንያት ነው።
  4. አላህ አንድን መንደር ሲያጠፋ በውስጧ ደጋጎችም ሊኖሩ ይችላሉ። እነዚህ ደጋጎች የትንሳኤ ቀን በሞቱበት መልካምነት ላይ ሆነው ነው የሚቀሰቀሱት። ምድራዊ ቅጣቱ እነሱንም ማካተቱ በመጪው አለም አይጎዳቸውም።