عن أبي هريرة رضي الله عنه: أن رسول الله صلى الله عليه وسلم قال:
«يَنْزِلُ رَبُّنَا تَبَارَكَ وَتَعَالَى كُلَّ لَيْلَةٍ إِلَى السَّمَاءِ الدُّنْيَا حِينَ يَبْقَى ثُلُثُ اللَّيْلِ الْآخِرُ، يَقُولُ: «مَنْ يَدْعُونِي فَأَسْتَجِيبَ لَهُ؟ مَنْ يَسْأَلُنِي فَأُعْطِيَهُ؟ مَنْ يَسْتَغْفِرُنِي فَأَغْفِرَ لَهُ؟».

[صحيح] - [متفق عليه]
المزيــد ...

ከአቡ ሁረይራ -አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸውና- እንደተላለፈው የአላህ መልክተኛ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም እንዲህ አሉ:
"የላቀውና ከፍ ያለው ጌታችን በሁሉም ሌሊት የመጨረሻ ሲሶ ወደ ቅርቢቱ ሰማይ ይወርዳል። እንዲህም ይላል 'ማን ነው የሚለምነኝ የምመልስለት? ማን ነው የሚጠይቀኝ ለርሱ የምሰጠው? ማን ነው ምህረትን ከኔ የሚፈልገው ለርሱ የምምረው?'"

Sahih/Authentic. - [Al-Bukhari and Muslim]

ትንታኔ

የጠራውና ከፍ ያለው አላህ በሁሉም ሌሊት የሌሊቱ የመጨረሻ ሲሶ ሲቀር ወደ ቅርቢቱ ሰማይ በመውረድ ባሮቹ እንዲለምኑት እንደሚያነሳሳ፤ እርሱ ለለመነው ተቀባይ፤ ለጠየቀው ሰጪ ነውና፤ የሚፈልጉትን እንዲጠይቁት የሚያነሳሳ፤ እርሱ ለአማኝ ባሮቹ መሀሪ ነውና ለወንጀሎቻቸውም ከርሱ ምህረትን እንዲፈልጉ የሚያብረታታቸው መሆኑን ነቢዩ ሶለሏሁ ዓለይሂ ወሰለም ገለፁ።

ትርጉም: እንግሊዝኛ ፈረንሳይኛ ስፔንኛ ቱርክኛ የኡርዱ ቋንቋ ኢንዶኔዥያኛ ቦስንያኛ ሩስያኛ ባንጋሊኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ታጋሎግ ህንድኛ ቬትናማዊ ሲንሃላዊ ኡይጙራዊ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ማላያላምኛ ቴልጉ ስዋሒልኛ ታሚልኛ ቦርምኛ ታይላንድኛ ጃፓንኛ ቡሽትኛ አሳምኛ አልባንኛ السويدية الهولندية الغوجاراتية الدرية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. የሌሊቱ የመጨረሻው ሲሶ ትሩፋቱንና በዚህ ወቅት ሶላት መስገድ ፣ ዱዓእ ማድረግና ምህረትን መፈለግ ያለውን ደረጃ እንረዳለን።
  2. አንድ ሰው ይህንን ሐዲሥ በሚሰማበት ጊዜ ዱዓእ ተቀባይነት የሚገኝበት ወቅትን በመሸመት ላይ እጅግ የሚጓጓ ሊሆን ይገባል።
ተጨማሪ