عَنْ عُبَادَةَ رَضِيَ اللَّهُ عَنْهُ عَنِ النَّبِيِّ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ قَالَ:
«مَنْ شَهِدَ أَنْ لَا إِلَهَ إِلَّا اللهُ وَحْدَهُ لَا شَرِيكَ لَهُ، وَأَنَّ مُحَمَّدًا عَبْدُهُ وَرَسُولُهُ، وَأَنَّ عِيسَى عَبْدُ اللهِ وَرَسُولُهُ وَكَلِمَتُهُ أَلْقَاهَا إِلَى مَرْيَمَ وَرُوحٌ مِنْهُ، وَالْجَنَّةُ حَقٌّ، وَالنَّارُ حَقٌّ، أَدْخَلَهُ اللهُ الْجَنَّةَ عَلَى مَا كَانَ مِنَ الْعَمَلِ».

[صحيح] - [متفق عليه]
المزيــد ...

ከዑባዳ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) እንዲህ ብለዋል:
"ከአላህ በስተቀር በእውነት የሚመለክ አምላክ እንደሌለ፤ ብቸኛና አጋርም እንደሌለው፤ ሙሐመድም የአላህ ባሪያና መልክተኛው መሆናቸውን፤ ዒሳም የአላህ ባሪያና መልክተኛው፣ ወደመርየምም ያስተላለፈው ቃሉና ከርሱ የሆነ መንፈስ መሆኑን፣ ጀነትም እውነት መሆኗን፣ እሳትም እውነት መሆኗን የመሰከረ ሰው በማንኛውም ስራ ላይ ሆኖም አላህ ጀነት ያስገባዋል።"

Sahih/Authentic. - [Al-Bukhari and Muslim]

ትንታኔ

የአላህ መልክተኛ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) እየነገሩን ያለው: የተውሒድን ቃል ትርጉሙን አውቆ የሚያስፈርደውንም በመስራት የተናገረ ሰው፤ እንዲሁም በሙሐመድም (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ባርነትና መልክተኝነት የመሰከረ፤ የዒሳን ባርነትና መልክተኝነት ያመነ፤ አላህ ዒሳን "ሁን" በሚለው ቃሉ እንደፈጠራቸውና አላህ ከፈጠራቸው ነፍሶች መካከል አንዱ ነፍስ እንደሆኑም የመሰከረ፤ አይሁዶች ወደርሷ ካስጠጉት ዘለፋም እናቱን መርየምን ያጠራ፤ መኖራቸውንና የአላህ ፀጋና ቅጣቱ መሆናቸውን ከማመን ጋር ጀነትም እውነት መሆኑን፣ እሳትም እውነት መሆናቸውን ያመነ ሰው በአምልኮዎች ላይ ያጓደለና ወንጀሎችም ያሉበት ቢሆን እንኳ በዚህ እምነት ላይ ከሞተ መመለሻው ወደ ጀነት ነው።

ትርጉም: እንግሊዝኛ ፈረንሳይኛ ስፔንኛ ቱርክኛ የኡርዱ ቋንቋ ኢንዶኔዥያኛ ቦስንያኛ ሩስያኛ ባንጋሊኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ታጋሎግ ህንድኛ ቬትናማዊ ሲንሃላዊ ኡይጙራዊ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ማላያላምኛ ቴልጉ ስዋሒልኛ ታሚልኛ ቦርምኛ ታይላንድኛ ጀርመንኛ ጃፓንኛ ቡሽትኛ አሳምኛ አልባንኛ السويدية الهولندية الغوجاراتية الدرية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. ከፍ ያለው አላህ የመርየም ልጅ ዒሳን "ሁን" በሚለው ቃሉ ብቻ ያለ አባት ነው የፈጠራቸው።
  2. ዒሳና ሙሐመድ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእነርሱ ላይ ይስፈንና) የአላህ ባሪያዎችና መልዕክተኛዎች በመሆናቸው የማይስተባበሉ መልክተኞችና የማይመለኩ ባሪያዎች መሆናቸውን እንረዳለን።
  3. የተውሒድን ትሩፋትና ወንጀሎችን እንደሚያስምር እንረዳለን። ተውሒድን የያዘ ሰውም ከፊል ወንጀል ላይ ቢወድቅ እንኳ መመለሻው ጀነት ነው።
ተጨማሪ