عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ رضي الله عنه أَنَّهُ قَالَ:
قيل يا رسول الله من أسعد الناس بشفاعتك يوم القيامة؟ قال رسول الله صلى الله عليه وسلم: «لقد ظننت يا أبا هريرة ألا يسألني عن هذا الحديث أحد أول منك لما رأيت من حرصك على الحديث، أسعد الناس بشفاعتي يوم القيامة، من قال لا إله إلا الله، خالصًا من قلبه أو نفسه».

[صحيح] - [رواه البخاري]
المزيــد ...

አቢ ሁረይራ ረዲየሏሁ ዓንሁ እንዲህ ማለታቸው ተላልፏል፡
"የአላህ መልእክተኛ ሆይ! የቂያማ ቀን በርሶ ምልጃ ከሰዎች ሁሉ ይበልጥ እድለኛው ማን ነው?" ተባሉ። የአላህ መልዕክተኛም ሶለላሁ ዓለይሂ ወሰለም እንዲህ አሉ፡- 'አቡ ሁረይራ ሆይ! ባንተ ላይ ካየሁት የሓዲሥ ጉጉት አንፃር ይህንን ጥያቄ ለመጠየቅ የሚቀድምህ አይኖርም ብዬ አስቤ ነበር። የቂያማ ቀን በኔ አማላጅነት ከሰዎች ሁሉ ይበልጥ እድለኛ የሚሆኑት ጥርት ባለ መልኩ ከልባቸው ወይም ከውስጣቸው 'ላ ኢላሃ ኢለሏህ' ያሉት ናቸው።'"

Sahih/Authentic. - [Al-Bukhari]

ትንታኔ

ነቢዩ ﷺ የትንሳኤ ቀን በምልጃቸው ከሰዎች ሁሉ የበለጠ እድለኛ የሚሆኑት "ከልባቸው ወይም ከውስጣቸው 'ላ ኢላሃ ኢለሏህ' ያሉት" ማለትም ከአሏህ በቀር በእውነት አምልኮ የሚገባው እንደሌለ አምነው ከሽርክ ይሁን ከይዩልኝና ይስሙልኝም ጥርት ያሉት መሆናቸውን እየነገሩን ነው።

ትርጉም: እንግሊዝኛ ፈረንሳይኛ ስፔንኛ ቱርክኛ የኡርዱ ቋንቋ ኢንዶኔዥያኛ ቦስንያኛ ሩስያኛ ባንጋሊኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ታጋሎግ ህንድኛ ቬትናማዊ ሲንሃላዊ ኡይጙራዊ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ማላያላምኛ ቴልጉ ስዋሒልኛ ታሚልኛ ቦርምኛ ታይላንድኛ ጀርመንኛ ጃፓንኛ ቡሽትኛ አሳምኛ አልባንኛ السويدية الهولندية الغوجاراتية الدرية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. ነብዩ ﷺ አኼራ ላይ ሸፋዓ እንደሚያደርጉና ሸፋዓቸውም ተውሒድ ላላቸው ሰዎች መሆኑን ያፀድቃል፤
  2. የነቢዩ ﷺ ሸፋዓ ተውሒድ ላይ እያለ ጀሀነም የተፈረደበትን ወደ ጀሀነም እንዳይገባ፤ ከገባ ደግሞ እንዲወጣ የሚያደርጉት ምልጃ ነው፤
  3. ለአላህ ጥርት ተደርጋ የተባለች የተውሒድ ቃል ያላት ትሩፋትና የምታሳድረው ከፍተኛ ፋና፤
  4. የተውሒድ ቃል የሚረጋገጠው ትርጉሟን በማወቅና በምታስፈርደው ተግባራዊ በማድረግ ነው፤
  5. አቢ ሁረይራ ያለውን ደረጃና በእውቀት ላይ ያለውን ጉጉት እንረዳለን።