عَن عُمَرَ بنِ الخَطَّابِ رَضِيَ اللَّهُ عَنْهُ قال: سَمِعْتُ النَّبِيَّ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ يَقُولُ:
«لَا تُطْرُونِي كَمَا أَطْرَتِ النَّصَارَى ابْنَ مَرْيَمَ؛ فَإِنَّمَا أَنَا عَبْدُهُ، فَقُولُوا: عَبْدُ اللهِ وَرَسُولُهُ».

[صحيح] - [رواه البخاري]
المزيــد ...

ዑመር ኢብኑል ኸጧብ ረዲየሏሁ ዓንሁ እንዲህ ብለዋል፡ "የአሏህ መልዕክተኛ ሶለሏሁ ዓለይሂ ወሰለም እንዲህ ሲሉ ሰምቻቸዋለሁ፡
'ክርስቲያኖች የመርየም ልጅን ሲያሞግሱ ወሰን እንዳለፉት እኔን ስታሞግሱ ወሰን አትለፉ። እኔ የአሏህ ባሪያ ብቻ ነኝ። ስለዚህም የአላህ ባሪያና መልክተኛው በሉኝ።'"

Sahih/Authentic. - [Al-Bukhari]

ትንታኔ

ክርስቲያኖች ዒሳ ዓለይሂ ሰላምን በተመለከተ ወሰን እንዳለፉት ሁሉ ነቢዩም ሶለሏሁ ዓለይሂ ወሰለም ህዝባቸው እሳቸውን በማሞገስ በኩል፣ በአላህ ባህሪያትና ልዩ ድርጊቶቹ እሳቸውን በመግለፅ፣ የሩቅ እውቀትን እንደሚያውቁ በመሞገት፣ ወይም ከአሏህ ጋር እሳቸውን በመማፀንና በመሳሰሉት መልኩ ወሰን እንዳይታለፍባቸው አስጠነቀቁ። ከዚያም ከአሏህ ባርያዎች መካከል አንዱ መሆናቸውን ገልፀው፤ እሳቸውን "የአሏህ ባርያውና መልዕክተኛው" ብለን እንድንገልፃቸው አሳሰቡ።

ትርጉም: እንግሊዝኛ ፈረንሳይኛ ስፔንኛ ቱርክኛ የኡርዱ ቋንቋ ኢንዶኔዥያኛ ቦስንያኛ ሩስያኛ ባንጋሊኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ታጋሎግ ህንድኛ ቬትናማዊ ሲንሃላዊ ኡይጙራዊ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ማላያላምኛ ቴልጉ ስዋሒልኛ ታሚልኛ ቦርምኛ ታይላንድኛ ጀርመንኛ ጃፓንኛ ቡሽትኛ አሳምኛ አልባንኛ السويدية الهولندية الغوجاراتية الدرية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. ወደ ሽርክ የሚያደርስ በመሆኑ በማላቅ እና በማወደስ ረገድ ሸሪዓ የደነገገውን ገደብ ከማለፍ መጠንቀቅ እንደሚገባ፤
  2. ይህ ነቢዩ ሶለላሁ ዓለይሂ ወሰለም ያስጠነቀቁት ነገር በእውነቱ በዚህ ኡማ ተከስቷል። ይህም የተወሰኑት ነብዩ ﷺ ላይ፣ ከፊሎች የነቢዩ ﷺ ቤተሰቦች ላይ፣ ሌሎች ደግሞ ወልዮች ላይ ይህ ያስጠነቀቁትን ነገር በመፈፀም ሽርክ ላይ አርፈዋል።
  3. የአላህ መልእክተኛ ሶለላሁ ዓለይሂ ወሰለም የአሏህ ባሪያው ናቸው እንጂ ከአምላክ መለያዎች መካከል የትኛውም እንደማይገባቸው ለመጠቆም ራሳቸው የአላህ ባሪያ መሆናቸውን ገለፁ።
  4. ረሱል ሶለሏሁ ዓለይሂ ወሰለም ከአሏህ የተላኩ መልዕክተኛው በመሆናቸው ሊያምኗቸውና ሊከተሏቸው እንደሚገባ ለመጠቆም ራሳቸውን የአሏህ መልዕክተኛ መሆናቸውንም ገለፁ።