عن عبد الله بن مسعود قال: قال رسول الله صلى الله عليه وسلم:
«هلك المُتَنَطِّعُون» قالها ثلاثًا.

[صحيح] - [رواه مسلم]
المزيــد ...

ዓብደሏህ ቢን መስዑድ ረዲየሏሁ ዓንሁ እንዲህ ማለቱ ተላልፏል፡ "የአሏህ መልዕክተኛ ሶለሏሁ ዓለይሂ ወሰለም እንዲህ አሉ፡
'ፅንፈኞች ጠፉ!' ሶስት ጊዜ ደጋገሟት።"

Sahih/Authentic. - [Muslim]

ትንታኔ

ነቢዩ ﷺ ያመጡትን ሸሪዓዊ ወሰን ያለ ምንም መመሪያና እውቀት ወሰን ተላልፈው በንግግራቸውም ይሁን በተግባራቸው በእምነታቸውም ይሁን በአለማዊ ጉዳያቸው ፅንፍ የሚረግጡ ሰዎች ያለባቸውን ውርደትና ኪሳራ ተናገሩ።

ትርጉም: እንግሊዝኛ ፈረንሳይኛ ስፔንኛ ቱርክኛ የኡርዱ ቋንቋ ኢንዶኔዥያኛ ቦስንያኛ ሩስያኛ ባንጋሊኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ታጋሎግ ህንድኛ ቬትናማዊ ሲንሃላዊ ኡይጙራዊ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ማላያላምኛ ቴልጉ ስዋሒልኛ ታሚልኛ ቦርምኛ ታይላንድኛ ጀርመንኛ ጃፓንኛ ቡሽትኛ አሳምኛ አልባንኛ السويدية الهولندية الغوجاراتية الدرية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. በየትኛውም ጉዳይ በተለይም በዒባዳና ፃድቃንን በማላቅ ረገድ ወሰን ማለፍና ያላቅም መንጠራራት መከልከሉ፤ ከእንዲህ አይነቱ ነገር መራቁ በየትኛውም ጉዳይ ላይ እንደሚበረታታ፤
  2. በአምልኮም ይሁን በሌላው ጉዳይ ተስተካክሎ የተሟላውን መፈለግ እንደሚገባ፤ ይህም የሚሆነው ሸሪዓውን በመከተል መሆኑ፤
  3. አሳሳቢ ጉዳይ ላይ ጠንከር ማድረግ እንደሚገባ፤ ምክንያቱም ነቢዩ ﷺ ይህንኑ እንኳ ሲናገሩ ሶስት ጊዜ ደጋግመው ነውና የተናገሩት።
  4. የእስልምና ገራገርነትና ቀላልነትን እንረዳለን።