عن أبي الهيَّاج الأسدي قال:
قَالَ لِي ‌عَلِيُّ بْنُ أَبِي طَالِبٍ: أَلَا أَبْعَثُكَ عَلَى مَا بَعَثَنِي عَلَيْهِ رَسُولُ اللهِ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ؟ أَنْ لَا تَدَعَ تِمْثَالًا إِلَّا طَمَسْتَهُ، وَلَا قَبْرًا مُشْرِفًا إِلَّا سَوَّيْتَهُ.

[صحيح] - [رواه مسلم]
المزيــد ...

ከአቢል ሀያጅ አልአሰዲይ እንደተላለፈው እንዲህ አለ:
"ዐሊይ ቢን አቢ ጧሊብ ለኔ እንዲህ አለኝ: 'የአላህ መልክተኛ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም በላኩኝ ነገር ላይ ልላክህን? ማንኛውም ምስልን (ስታገኝ) ያስወገድከው ቢሆን እንጂ ላትተወው ነው፤ ማንኛውም ከፍ ያለ ቀብርንም ያስተካከልከው ቢሆን እንጂ ላትተወው ነው።'"

Sahih/Authentic. - [Muslim]

ትንታኔ

ነቢዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ሶሓቦቻቸውን "ምስልን" (እሱም አካል ይኑረውም አይኑረው የነፍስ ያለው ነገር ምስል ነው።) ያስወገዱት ወይም ያወደሙት ቢሆን እንጂ እንዳይተዉት ይልኩ ነበር።
ከፍ ያለ ቀብርንም ከምድር ጋር እኩል ያደረጉትና በላዩ ላይ የተገነባውንም ያወደሙ ወይም ከመሬት ብዙም ከፍ ሳይል አንድ ስንዝር ብቻ ከፍ በማድረግ ያስተካከሉት ቢሆን እንጂ እንዳይተዉት ይልኩ ነበር።

ትርጉም: እንግሊዝኛ ፈረንሳይኛ ስፔንኛ ቱርክኛ የኡርዱ ቋንቋ ኢንዶኔዥያኛ ቦስንያኛ ሩስያኛ ባንጋሊኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ህንድኛ ቬትናማዊ ሲንሃላዊ ኡይጙራዊ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ማላያላምኛ ቴልጉ ስዋሒልኛ ታሚልኛ ቦርምኛ ታይላንድኛ ጀርመንኛ ጃፓንኛ ቡሽትኛ አሳምኛ አልባንኛ السويدية الهولندية الغوجاراتية الدرية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. ነፍስ ያላቸው ነገራቶችን ምስል ማድረግ ወደ ሺርክ ስለሚያዳርስ ክልክል መሆኑን እንረዳለን።
  2. ስልጣን ወይም አቅም ላለው ሰው መጥፎን ነገር በእጅ ማስወገዱ መደንገጉን ፤
  3. ስዕላ ስእሎች፣ ቅርፃ ቅርፆችና ቀብር ላይ መገንባትን የመሳሰሉ ወደ ጃሂሊያ ዘመን ፈለጎች የሚጠቁሙ ነገሮችን ሁሉ በማስወገድ ላይ የነቢዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለምን ጉጉት እንረዳለን።