عن خَوْلَةَ بِنْتَ حَكِيمٍ السُّلَمِيَّةَ قَالتْ: سَمِعْتُ رَسُولَ اللهِ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ يَقُولُ:
«مَنْ نَزَلَ مَنْزِلًا ثُمَّ قَالَ: أَعُوذُ بِكَلِمَاتِ اللهِ التَّامَّاتِ مِنْ شَرِّ مَا خَلَقَ، لَمْ يَضُرَّهُ شَيْءٌ حَتَّى يَرْتَحِلَ مِنْ مَنْزِلِهِ ذَلِكَ».

[صحيح] - [رواه مسلم]
المزيــد ...

ከኸውለህ ቢንት ሐኪም አስሱለሚየህ እንደተላለፈው እንዲህ አለች: "የአላህ መልክተኛ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም እንዲህ ሲሉ ሰምቻለሁ:
"በአንድ ስፍራ ላይ አርፎ ከዚያም ‹አዑዙ ቢከሊማቲላሂ አትታማቲ ሚን ሸሪ ማ ኸለቀ (ምሉዕ በሆኑ የአላህ ቃላት ከፈጠራቸው ጎጂ ነገሮች እጠበቃለሁ)› ያለ ሰው ከዛ ስፍራ እስኪንቀሳቀስ ድረስ አንዳችም አይጎዳውም።"

Sahih/Authentic. - [Muslim]

ትንታኔ

ነቢዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም የሰው ልጅ አንድ ስፍራ ላይ በሚያርፍበት ጊዜ የሚፈራቸውን ሁሉ አስፈሪ ነገሮች የሚከላከልበትን ጠቃሚ መጠበቂያና መጠጊያ ለኡመታቸው እየጠቆሙ ነው። ይህም ጉዞም ላይ ይሁን ሊዝናናም ይሁን ወይም ከዛ ውጪ ባረፈበት ስፍራ ላይ ከሚገኝ ፍጡራን ሁሉ ክፋት በትሩፋቱ፣ በበረከቱና በጥቅሙ የተሟላ በሆነውና ከሁሉም ነውርና ጉድለት የፀዳ በሆነው የአላህ ቃል ከተጠበቀና ከተጠጋ በዛ ስፍራ እስካለ ድረስ ከሁሉም ጎጂ ነገሮች ደህንነቱ ይጠበቃል።

ትርጉም: እንግሊዝኛ ፈረንሳይኛ ስፔንኛ ቱርክኛ የኡርዱ ቋንቋ ኢንዶኔዥያኛ ቦስንያኛ ሩስያኛ ባንጋሊኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ህንድኛ ቬትናማዊ ሲንሃላዊ ኡይጙራዊ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ማላያላምኛ ቴልጉ ስዋሒልኛ ታሚልኛ ቦርምኛ ታይላንድኛ ጀርመንኛ ጃፓንኛ ቡሽትኛ አሳምኛ አልባንኛ السويدية الهولندية الغوجاراتية الدرية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. በአላህ መጠበቅ አምልኮ ነው። የተፈቀደ የሚሆነውም በአላህ ወይም በስሞቹና በባህሪያቶቹ ሲጠበቅ ነው።
  2. ከአላህ ባህሪያቶች መካከል አንዱ በሆነው የአላህ ቃል መጠበቅ እንደሚፈቀድ እንረዳለን። ይህም በማንኛውም ፍጡር ከመጠበቅ ተቃራኒ ሲሆን ከአላህ ውጪ ካለ አካል ጥበቃን መሻት ሺርክ ነው።
  3. የዚህ ዱዓእ ትሩፋትና በረከትን እንረዳለን።
  4. በዚክሮች መመሸግ (መከላከል) ሰው ከክፋቶች እንዲጠበቅ አንዱ ሰበብ ነው።
  5. በጋኔን ፣ በጠንቋይ፣ በአታላዮችና በሌሎችም ከአላህ ውጪ ባሉ አካላት ጥበቃ መፈለግ ውድቅ መደረጉ፤
  6. ይህ ዱዓእ በሀገሩም ይሁን በጉዞ አንድ ስፍራ ላይ ላረፈ ሰው መደንገጉን እንረዳለን።