عن عائشة رضي الله عنها قالت: قال النبي صلى الله عليه وسلم:
«لَا تَسُبُّوا الْأَمْوَاتَ، فَإِنَّهُمْ قَدْ أَفْضَوْا إِلَى مَا قَدَّمُوا».

[صحيح] - [رواه البخاري]
المزيــد ...

ከእናታችን ዓኢሻህ -አላህ መልካም ስራዋን ይውደድላትና- እንደተላለፈው እንዲህ አለች: ነቢዩ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም እንዲህ አሉ:
"ሟቾችን አትሳደቡ! እነርሱ ወዳስቀደሙት (ስራቸው) ሂደዋልና።"

Sahih/Authentic. - [Al-Bukhari]

ትንታኔ

ነቢዩ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ሟቾችን መሳደብና ክብራቸውን መንካት ክልክል መሆኑን አብራሩ። ከእኩይ ስነ ምግባሮችም የሚመደብ እንደሆነ ገለፁ። ምክንያቱም ይህ ስድብ በህይወት ያሉ ሰዎችን ከመጉዳት የዘለለ ለነርሱ የማይደርሳቸው ከመሆኑም በተጨማሪ እነሱ ወዳስቀደሙት መልካምም ይሁን መጥፎ ስራቸው ደርሰዋልና።

ትርጉም: እንግሊዝኛ ፈረንሳይኛ ስፔንኛ ቱርክኛ የኡርዱ ቋንቋ ኢንዶኔዥያኛ ቦስንያኛ ሩስያኛ ባንጋሊኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ታጋሎግ ህንድኛ ቬትናማዊ ሲንሃላዊ ኡይጙራዊ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ማላያላምኛ ቴልጉ ስዋሒልኛ ታሚልኛ ቦርምኛ ታይላንድኛ ጀርመንኛ ጃፓንኛ ቡሽትኛ አሳምኛ አልባንኛ السويدية الهولندية الغوجاراتية الدرية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. ሐዱሡ ሟቾችን መሳደብ ክልክል መሆኑን ይጠቁማል።
  2. ሟቾችን ከመሳደብ መታቀብ የህያው ሰዎችን ጥቅምም የማህበረሰቡንም ሰላም ከመጣላትና ከመናቆር ይጠብቃል።
  3. ሟቾችን ከመሳደብ የመከልከሉ ጥበብ ወዳስቀደሙት ስራ ስለደረሱ መስደቡ ከንቱ ስለሆነና በተጨማሪ የህያው ቅርብ ዘመዶቹን ስለሚያውክ ነው።
  4. የሰው ልጅ ጥቅም የሌለውን ነገር መናገር አይገባውም።