عن أبي هريرة رضي الله عنه أن رسول الله صلى الله عليه وسلم كان يقول:
«الصَّلَوَاتُ الْخَمْسُ، وَالْجُمُعَةُ إِلَى الْجُمُعَةِ، وَرَمَضَانُ إِلَى رَمَضَانَ، مُكَفِّرَاتٌ مَا بَيْنَهُنَّ إِذَا اجْتَنَبَ الْكَبَائِرَ».

[صحيح] - [رواه مسلم]
المزيــد ...

ከአቢ ሁረይራ ረዲየሏሁ ዓንሁ እንደተላለፈው ነቢዩ ﷺ እንዲህ ይሉ ነበር፡
"ከባባዶቹን ወንጀሎች ይጠንቀቁ እንጂ አምስቱ ሶላቶች፣ ከጁሙዐ እስከ ጁሙዐ፣ ከረመዿን እስከ ረመዿን በመካከላቸው የተሰሩትን ወንጀሎች ያስሰርዛሉ።"

Sahih/Authentic. - [Muslim]

ትንታኔ

ነቢዩ ﷺ ከባባዶቹን ወንጀሎች መጠንቀቅ እንደቅድመ መስፈርት ከተሟላ አምስቱ በቀንና ሌሊት የሚከናወኑት ሶላቶች፣ በየሳምንቱ የሚሰገደው የጁምዐ ሶላትና በየአመቱ የረመዿንን ወር መፆም በመካከላቸው የሚፈፀምን ትናንሽ ወንጀሎችን እንደሚያስምሩ ነገሩን። ዝሙትና መጠጥን የመሰሉ ከባባድ ወንጀሎች በተውባ ካልሆነ በቀር አይሰረዙም።

ትርጉም: እንግሊዝኛ ፈረንሳይኛ ስፔንኛ ቱርክኛ የኡርዱ ቋንቋ ኢንዶኔዥያኛ ቦስንያኛ ሩስያኛ ባንጋሊኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ታጋሎግ ህንድኛ ቬትናማዊ ሲንሃላዊ ኡይጙራዊ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ማላያላምኛ ቴልጉ ስዋሒልኛ ታሚልኛ ቦርምኛ ታይላንድኛ ጀርመንኛ ጃፓንኛ ቡሽትኛ አሳምኛ አልባንኛ السويدية الهولندية الغوجاراتية الدرية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. ከወንጀሎች መካከል ከባባድና ትናንሽ የሚባሉ እንዳሉ፤
  2. ትናንሽ ወንጀሎች የሚሰረዙት ከባባዶቹን ወንጀሎች መራቅን እንደመስፈርት ማሟላት ከተቻለ መሆኑን እንረዳለን።
  3. ከባባድ ወንጀሎች የሚባሉት ወይ በዱኒያ ቅጣት የተወሰነባቸው፣ ወይም በአኼራ የሚያስከትሉትን የቅጣት አይነት የተነገረባቸው፣ ወይም የአላህ ቁጣ የመጣባቸው፣ ወይም ከባድ ዛቻ ያለባቸው፣ ወይም ደግሞ አድራጊው የተረገመባቸው ሲሆኑ ነው። ለምሳሌ፡ ዝሙት፣ መጠጥ መጠጣት ይጠቀሳሉ።