عن عائشة رضي الله عنها قالت: قال رسول الله صلى الله عليه وسلم:
«السِّوَاكُ مَطْهَرَةٌ لِلْفَمِ، مَرْضَاةٌ لِلرَّبِّ».

[صحيح] - [رواه النسائي وأحمد] - [مسند أحمد: 24203]
المزيــد ...

ከዓኢሻህ ረዲየሏሁ ዐንሃ እንደተላለፈው እንዲህ አለች፡ "የአሏህ መልክተኛ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና እንዲህ ብለዋል፡
'ሲዋክ አፍን የሚያጠራ (የሚያፀዳ)፤ የአሏህንም ውዴታ የሚያስገኝ ነው።'"

[ሶሒሕ ነው።] - [ነሳኢና አሕመድ ዘግበውታል።] - [ሙስነድ አሕመድ - 24203]

ትንታኔ

ነቢዩ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና አራክ በተባለው ወይም በአምሳያው በሆነ መፋቂያ ጥርስን መፋቅ አፍን ከቆሻሻ እና ከመጥፎ ጠረን እንደሚያፀዳ ነገሩን። ይህንኑ ማድረግም ለአሏህ ታዛዥነትና ለትእዛዙ ምላሽ መስጠት ከመሆኑ ባሻገር አሏህ የሚወደውን ንፅህናንም የሚያስተርፍ ስለሆነ ድርጊቱ የአሏህን ውዴታ ማግኛ ሰበብ መሆኑን ነገሩን።

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. ጥርስን መፋቅ ያለውን ትሩፋትና ነቢዩም የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና ዑመታቸው ድርጊቱን ያበዛ ዘንድ ማነሳሳታቸውን እንረዳለን።
  2. ቢፍቁበት የተሻለው "አራክ" የተባለውን የዛፍ ግንድ (መፋቂያ) ከመሆኑም ጋር በምትኩ የጥርስ ብሩሽ ከሳሙናው ጋር መጠቀምም ይቻላል።
ትርጉሞችን ይመልከቱ
ቋንቋ: እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ ስፔንኛ ተጨማሪ (67)