عن أنس بن مالك رضي الله عنه أن رسول الله صلى الله عليه وسلم قال:
«مَنْ أَحَبَّ أَنْ يُبْسَطَ لَهُ فِي رِزْقِهِ، وَيُنْسَأَ لَهُ فِي أَثَرِهِ، فَلْيَصِلْ رَحِمَهُ».

[صحيح] - [متفق عليه]
المزيــد ...

ከአነስ ቢን ማሊክ -አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸውና- እንደተላለፈው የአላህ መልክተኛ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም እንዲህ አሉ:
"ሲሳዩ እንዲሰፋለትና እድሜው እንዲረዝምለት የወደደ ሰው ዝምድናውን ይቀጥል።"

Sahih/Authentic. - [Al-Bukhari and Muslim]

ትንታኔ

ነቢዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ቅርብ ዘመዶችን በመዘየር ፣ በአካላዊና ገንዘባዊ ጉዳይ በማገዝና በሌሎችም መልኩ ዝምድናን በመቀጠል ላይ አነሳሱ። በተጨማሪም ዝምድናን መቀጠል ለሲሳይ መስፋትና ለእድሜ መርዘም ምክንያት መሆኑንም ተናገሩ።

ትርጉም: እንግሊዝኛ ፈረንሳይኛ ስፔንኛ ቱርክኛ የኡርዱ ቋንቋ ኢንዶኔዥያኛ ቦስንያኛ ሩስያኛ ባንጋሊኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ህንድኛ ቬትናማዊ ሲንሃላዊ ኡይጙራዊ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ማላያላምኛ ቴልጉ ስዋሒልኛ ታሚልኛ ቦርምኛ ታይላንድኛ ጀርመንኛ ጃፓንኛ ቡሽትኛ አሳምኛ አልባንኛ السويدية الهولندية الغوجاراتية الدرية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. ዝምድና በማለት የተፈለገው በአባትና በእናት በኩል ያሉ ቅርብ ሰዎች ናቸው። እጅግ ቅርብ ዘመድ በሆኑ ቁጥር በዛው ልክ መቀጠሉም የተገባ ይሆናል።
  2. ምንዳ በስራው አምሳያ ነው የሚሰጠው። ዝምድናውን በበጎና መልካምነት የቀጠለ ሰውን አላህም እድሜውና ሲሳዩን ይቀጥልለታል።
  3. ዝምድናን መቀጠል ለሲሳይ መስፋትና መዘርጋት እንዲሁም ለእድሜ መርዘም ምክንያት ነው። ምንም እንኳ የመሞቻ ቀኑና ሲሳዩ የተወሰነ ቢሆን ባለው ሲሳይና እድሜ በረከት ይሰፍንበታል። የተሰጠውን እድሜ ሌላው ከሚጠቀምበት በላይ ይጠቀምበታል። በርግጥ የሲሳይና እድሜ መጨመሩ እውነተኛ መጨመር ነውም ተብሏል። አላህ እጅግ አዋቂ ነው!