عَنْ أَبِي الدَّرْدَاءِ رضي الله عنه أَنَّ النَّبِيَّ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ قَالَ:
«مَا شَيْءٌ أَثْقَلُ فِي مِيزَانِ الْمُؤْمِنِ يَوْمَ القِيَامَةِ مِنْ خُلُقٍ حَسَنٍ، وَإِنَّ اللَّهَ لَيُبْغِضُ الفَاحِشَ البَذِيءَ».

[صحيح] - [رواه أبو داود والترمذي]
المزيــد ...

ከአቡ ደርዳእ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው: ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) እንዲህ አሉ:
"የትንሳኤ ቀን ከመልካም ስነ ምግባር የበለጠ የአማኝን ሚዛን የሚደፋ አንድም ነገር የለም። አላህ ፀያፍ የሚሰራንና ፀያፍ የሚናገርን ይጠላል።"

Sahih/Authentic with its two versions. - [At-Tirmidhi]

ትንታኔ

ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) የትንሳኤ ቀን ከተግባሮችም ከንግግሮችም የአማኝን ሚዛን የሚደፋለት መልካም ስነ ምግባር መሆኑን ተናገሩ። ይህም ፊትን ፈታ በማድረግ፣ ሌላን ከመጉዳት በመቆጠብና መልካም ነገርን ለሌሎች በመለገስ ነው። የላቀው አላህ፤ በድርጊትም ይሁን በንግግር አፀያፊ የሆነንም በአንደበቱ ብልግና የሚናገርንም ሰው ይጠላል።

ትርጉም: እንግሊዝኛ ፈረንሳይኛ ስፔንኛ ቱርክኛ የኡርዱ ቋንቋ ኢንዶኔዥያኛ ቦስንያኛ ሩስያኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ህንድኛ ቬትናማዊ ሲንሃላዊ ኡይጙራዊ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ማላያላምኛ ስዋሒልኛ ቡሽትኛ አሳምኛ السويدية الهولندية الغوجاراتية الدرية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. የመልካም ስነ ምግባርን ትሩፋት እንረዳለን። መልካም ስነምግባር ባለቤቱን የአላህን ውዴታና የባሮቹን ውዴታ እንዲያገኝ ያበቃዋል። እርሱ የትንሳኤ ቀን ከሚመዘኑትም እጅግ ትልቁ ነው።