عن أبي هريرة رضي الله عنه أن رسول الله صلى الله عليه وسلم قال:
«أَتَدْرُونَ مَا الْغِيبَةُ؟»، قَالُوا: اللهُ وَرَسُولُهُ أَعْلَمُ، قَالَ: «ذِكْرُكَ أَخَاكَ بِمَا يَكْرَهُ»، قِيلَ: أَفَرَأَيْتَ إِنْ كَانَ فِي أَخِي مَا أَقُولُ؟ قَالَ: «إِنْ كَانَ فِيهِ مَا تَقُولُ فَقَدِ اغْتَبْتَهُ، وَإِنْ لَمْ يَكُنْ فِيهِ فَقَدْ بَهَتَّهُ».

[صحيح] - [رواه مسلم]
المزيــد ...

ከአቡ ሁረይራ -አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸውና- እንደተላለፈው የአላህ መልክተኛ ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም እንዲህ አሉ፡
"ሀሜት ምን እንደሆነ ታውቃላችሁን?" ሶሐቦችም "አላህና መልክተኛው ያውቃሉ።" አሉ። እሳቸውም "ወንድምህን በሚጠላው ነገር ማውሳትህ ነው።" አሉ። "የምናገረው ነገር ወንድሜ ላይ ካለስ (ሀሜት ይባላልን?)" ተብለው ተጠየቁ። እሳቸውም "የምትናገረው ነገር እሱ ላይ ካለ በርግጥ አምተሀዋል። እሱ ላይ ከሌለ ደግሞ በርግጥም ቀጥፈህበታል።"

Sahih/Authentic. - [Muslim]

ትንታኔ

ነቢዩ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም የተከለከለውን ሀሜት እውነታ : ሙስሊምን በሌለበት በሚጠላው ነገር ማውሳት መሆኑን አብራሩ። ይህም ተፈጥሯዊውም ሆነ ስነ ምግባሪያዊ ባህሪውን ቢያወሳ ተመሳሳይ ነው። እውሩ ፣ አጭበርባሪ ፣ ውሸታምና የመሳሰሉትን እሱ ላይ የሚገኙ የተወገዙ መገለጫዎችን በማውሳት ማማትን የመሳሰለው ነው።
እሱ ላይ የሌሉ ባህሪያት ከሆኑ ግን የተወሱት ከሀሜትም የባሰ ነው። እሱም መቅጠፍ (ቡህታን) ነው የሚሆነው :- ማለትም በሰው ላይ የሌሉበትን ባህሪያት መቅጠፍ ነው።

ትርጉም: እንግሊዝኛ ፈረንሳይኛ ስፔንኛ ቱርክኛ የኡርዱ ቋንቋ ኢንዶኔዥያኛ ቦስንያኛ ሩስያኛ ባንጋሊኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ታጋሎግ ህንድኛ ቬትናማዊ ሲንሃላዊ ኡይጙራዊ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ማላያላምኛ ቴልጉ ስዋሒልኛ ታሚልኛ ቦርምኛ ታይላንድኛ ጀርመንኛ ጃፓንኛ ቡሽትኛ አሳምኛ አልባንኛ السويدية الهولندية الغوجاراتية الدرية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. ነቢዩ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም እውቀትን ጥያቄያዊ በሆነ መንገድ ማስተላለፋቸውን ስናይ የሳቸው የማስተማር ስልት ውብ መሆኑን እንረዳለን ፤
  2. ሶሐቦች "አላህና መልክተኛው ያውቃሉ።" ማለታቸውን ስናይ ከነቢዩ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ጋር ያላቸው አደብ ውብ መሆኑን እንረዳለን ፤
  3. ተጠያቂ ስለማያውቀው ነገር "አላህ ያውቃል።" ማለት እንዳለበት እንረዳለን ፤
  4. ሸሪዐ ሐቆችን በመጠበቅና በማህበረሰቡ መካከል ወንድማማችነትን በመፍጠር ማህበረሰቡን መጠበቁን እንረዳለን ፤
  5. ሀሜት እንደአስፈላጊነቱ በአንዳንድ ሁኔታዎች ላይ ካልሆነ በስተቀር ክልክል ነው። ከነዚህም ውስጥ: - በደልን ለመከላከል : ይህም "እከሌ በድሎኛል ወይም በኔ ላይ እንዲህ ፈፅሟል።" በማለት ተበዳይ ሀቁን ማስመለስ የሚችል ሰው ዘንድ የበደለውን በማውሳት ነው። በትዳር ጉዳይ ወይም በሽርክና ወይም በጉርብትናና በመሳሰሉት ጉዳይ ለማማከር ሰውዬውን ማማት ከሚፈቀዱት መካከል የሚመደብ ነው።