عن عائشة رضي الله عنها عن النبي صلى الله عليه وسلم قال:
«إِنَّ أَبْغَضَ الرِّجَالِ إِلَى اللهِ الْأَلَدُّ الْخَصِمُ».

[صحيح] - [متفق عليه]
المزيــد ...

ከእናታችን ዓኢሻህ -አላህ መልካም ስራዋን ይውደድላትና- እንደተላለፈው ነቢዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም እንዲህ ብለዋል:
"ከሰዎች ሁሉ አላህ ዘንድ እጅግ የተጠላው ደረቅ ተከራካሪ የሆነ ሰው ነው።"

Sahih/Authentic. - [Al-Bukhari and Muslim]

ትንታኔ

የጠራውና ከፍ ያለው አላህ ከሰዎች ውስጥ ለእውነት እጅ መስጠትን የማይቀበል፣ እውነታውን በክርክሩ ለመመለስ የሚሞክር ወይም እውነትን ይዞ ቢከራከርም ነገር ግን ከሚዛናዊነት በሚያስወጣው መልኩ ክርክርን የሚያበዛና ያለ እውቀት የሚከራከርን ደረቅ ተከራካሪንና ክርክር የሚያበዛን እንደሚጠላ ነቢዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ተናገሩ።

ትርጉም: እንግሊዝኛ ፈረንሳይኛ ስፔንኛ ቱርክኛ የኡርዱ ቋንቋ ኢንዶኔዥያኛ ቦስንያኛ ሩስያኛ ባንጋሊኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ታጋሎግ ህንድኛ ቬትናማዊ ሲንሃላዊ ኡይጙራዊ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ማላያላምኛ ቴልጉ ስዋሒልኛ ታሚልኛ ቦርምኛ ታይላንድኛ ጀርመንኛ ጃፓንኛ ቡሽትኛ አሳምኛ አልባንኛ السويدية الهولندية الغوجاراتية الدرية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. ተበዳይ ሀቁን ሸሪዓዊ በሆነ መልኩ መክሰሱ የተወገዘ የሆነው የክርክር ይዘት ውስጥ አይገባም።
  2. ክርክርና ንትርክ በሙስሊሞች መካከል ልዩነትንና ጀርባ መሰጣጠትን የሚየስከትሉ የምላስ ወለምታዎች ናቸው።
  3. እውነትን ይዞና በጥሩ ዘይቤ ከሆነ ክርክር የተወደሰ ይሆናል። ውሸትን ለማፅናትና እውነትን ለመመለስ ከሆነ ወይም ያለማስረጃ ከሆነ ደግሞ የተወገዘ ክርክር ይሆናል።