عن المِقدام بن معدي كرب رضي الله عنه عن النبي صلى الله عليه وسلم قال:
«إِذَا أَحَبَّ الرَّجُلُ أَخَاهُ فَلْيُخْبِرْهُ أَنَّهُ يُحِبُّهُ».

[صحيح] - [رواه أبو داود والترمذي والنسائي في السنن الكبرى وأحمد]
المزيــد ...

ከሚቅዳም ቢን መዕዲከሪብ እንደተላለፈው ነቢዩ ሶለሏሁ ዓለይሂ ወሰለም እንዲህ ብለዋል:
"አንድ ሰው ወንድሙን ከወደደው እንደሚወደው ይንገረው።"

Sahih/Authentic. - [At-Tirmidhi]

ትንታኔ

ነቢዩ ሶለሏሁ ዓለይሂ ወሰለም በምእመናን መካከል ቁርኝታቸውን ከሚያጠናክሩ በመካከላቸውም ውዴታን ከሚያሰፍኑ ሰበቦች መካከል አንዱን ጠቀሱ። ይኸውም አንድ ሰው ወንድሙን የሚወደው ከሆነ እንደሚወደው ይንገረው አሉ።

ትርጉም: እንግሊዝኛ ፈረንሳይኛ ስፔንኛ ቱርክኛ የኡርዱ ቋንቋ ኢንዶኔዥያኛ ቦስንያኛ ሩስያኛ ባንጋሊኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ታጋሎግ ህንድኛ ቬትናማዊ ሲንሃላዊ ኡይጙራዊ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ማላያላምኛ ቴልጉ ስዋሒልኛ ታሚልኛ ቦርምኛ ታይላንድኛ ጀርመንኛ ጃፓንኛ ቡሽትኛ አሳምኛ አልባንኛ السويدية الهولندية الغوجاراتية الدرية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. ለአለማዊ ጥቅም ሳይሆን ጥርት ባለ መልኩ ለአሏህ ብሎ መውደድ ያለውን ደረጃ፤
  2. መዋደዱና መቆራኘቱ እንዲጨምር ለአሏህ ብለው የሚወዱትን እንደሚወዱት መንገር እንደሚበረታታ፤
  3. በምእመናን መካከል መዋደድ መንሰራፋቱ ኢማናዊ የሆነውን ወንድማማችነት እንደሚያጠነክርና ማህበረሰቡንም ከመለያየትና ከመበታተን እንደሚታደግ፤