عن جابر بن عبد الله رضي الله عنهما عن النبي صلى الله عليه وسلم قال:
«كُلُّ مَعْرُوفٍ صَدَقَةٌ».

[صحيح] - [رواه البخاري من حديث جابر، ورواه مسلم من حديث حذيفة]
المزيــد ...

ከጃቢር ቢን ዐብደላህ -አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸውና- እንደተላለፈው ነቢዩ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም እንዲህ ብለዋል:
"መልካም ነገሮች ሁሉ ምፅዋት ናቸው።"

Sahih/Authentic. - [Al-Bukhari]

ትንታኔ

በንግግርም ይሁን በተግባር ለሌሎች የምንውለው በጎነትና ጥቅም ሁሉ ምፅዋት እንደሚሆንና በሱም ምንዳና አጅር እንደምናገኝበት ነቢዩ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ተናገሩ።

ትርጉም: እንግሊዝኛ ፈረንሳይኛ ስፔንኛ ቱርክኛ የኡርዱ ቋንቋ ኢንዶኔዥያኛ ቦስንያኛ ሩስያኛ ባንጋሊኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ታጋሎግ ህንድኛ ቬትናማዊ ሲንሃላዊ ኡይጙራዊ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ማላያላምኛ ቴልጉ ስዋሒልኛ ታሚልኛ ቦርምኛ ታይላንድኛ ጀርመንኛ ጃፓንኛ ቡሽትኛ አሳምኛ አልባንኛ السويدية الهولندية الغوجاراتية الدرية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. ምፅዋት የሰው ልጅ ከገንዘቡ በሚያወጣው ላይ ብቻ የተገደበ ሳይሆን የሰው ልጅ ወደ ሌሎች በሚደርስ መልኩ የሚሰራውና የሚናገረውን ሁሉ መልካም ነገሮችን ያቀፈ ነው።
  2. በዚህ ሀዲስ ውስጥ ለመልካምና ለሌሎች ጥቅም ላለው ነገር ሁሉ መልፋትን ያነሳሳል።
  3. ትንሽም እንኳን ብትሆን ከመልካም ነገር አንዳችም ማሳነስ እንደማይገባ እንረዳለን።