+ -

عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ رضي الله عنه أَنَّ رَسُولَ اللهِ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ قَالَ:
«لَا تَبْدَؤوا الْيَهُودَ وَلَا النَّصَارَى بِالسَّلَامِ، فَإِذَا لَقِيتُمْ أَحَدَهُمْ فِي طَرِيقٍ فَاضْطَرُّوهُ إِلَى أَضْيَقِهِ».

[صحيح] - [رواه مسلم] - [صحيح مسلم: 2167]
المزيــد ...

ከአቡ ሁረይራ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው: የአላህ መልክተኛ (ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና እንዲህ ብለዋል:
"አይሁዶችንና ክርስቲያኖችን በሰላምታ አትጀምሯቸው። ከመካከላቸው አንዱን መንገድ ላይ ባገኛችሁ ጊዜም ወደ ጠባቡ መንገድ አጣብቡት።"

[ሶሒሕ ነው።] - [ሙስሊም ዘግበውታል።] - [ሶሒሕ ሙስሊም - 2167]

ትንታኔ

ነቢዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና ከአይሁዶችና ከክርስቲያኖች ውጪ ያለ ከሃዲ ይቅርና እነርሱን ራሱ በቃልኪዳን የሚኖሩ እንኳን ቢሆኑ ለነርሱ ቀድሞ ሰላምታ ማቅረብን ከለከሉ። ነቢዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና ከነርሱ መካከል አንዱን መንገድ ላይ ስናገኘው ወደ ጠባቡ መንገድ እንድናስጠጋው ገለፁ። መሃል መንገዱን ይዞ መሄድ ያለበት አማኝ ነው። ከመሃል መንገድ ዘወር የሚለው ከሃዲው ነው። በማንኛውም ሁኔታ ቢሆን ሙስሊም የተናነሰ መሆን የለበትም።

ትርጉም: እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ ስፔንኛ ኢንዶኔዥያኛ ፈረንሳይኛ ቱርክኛ ሩስያኛ ቦስንያኛ ሲንሃላዊ ህንድኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ቬትናማዊ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ስዋሒልኛ ቡሽትኛ አሳምኛ الهولندية الغوجاراتية Oromisht
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. አንድ ሙስሊም አንድን አይሁድ ወይም ክርስቲያን ወይ ሌላም እምነት ተከታይ የሆነ ከሃዲን ቀድሞ በሰላምታ መጀመሩ አይፈቀድለትም።
  2. እነርሱ ሰላምታውን ከጀመሩ "ወዐለይኩም" በማለት ለነርሱ ሰላምታን መመለስ ይፈቀዳል።
  3. አንድ ሙስሊም ከሃዲያንን ሆን ብሎ ማወክ አይፈቀድለትም። ለምሳሌ ወደ ጠባቡ መንገድ እንዲሄድ አስገዳጅ ነገሮች ሳይኖሩ ሆን ብሎ ማጣበብን ይመስል። ነገር ግን መንገዱ ጠባብ ወይም የተጨናነቀ ከሆነ በዛ መንገድ ቀድሞ የማለፍ መብት ያለው ሙስሊሙ ነው።
  4. ከሀዲው ዘወር ይበልለት።
  5. ያለምንም ግፍ ወይም በንግግር ሳናስቀይም የሙስሊሞች የበላይነትና የሌሎች ደግሞ መተናነስ ግልፅ መሆን እንዳለበት እንረዳለን።
  6. ከሃዲያንን በአላህ ላይ ባላቸው ክህደት ምክንያት ማጣበብ የመስለማቸው ምክንያት ሊሆንም ይችላል። ይህ ምክንያቱን እንዲያውቁ ካደረጋቸው ሰልመው ከእሳት እንዲድኑ ምክንያት ሊሆናቸው ይችላል።
  7. አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ አንድ ሙስሊም ለከሃዲ ቀድሞ እንዴት ነህ? ደህና አደርክ? ደህና አመሸህ?ና የመሳሰሉትን ማለቱ ችግር የለም። ክልከላው የሚተረጎመው በሰላምታ (አሰላሙ ዓለይኩም ማለት) ላይ ነው።
  8. ጢቢይ እንዲህ ብለዋል: «የቢድዓ ሰውም ቀደም ተብሎ በሰላምታ አይጀመርም የሚለው ተመራጭ አቋም ነው። የማያውቀውን ሰው ሰላምታ ጀምሮ በቃልኪዳን የሚኖር ከሃዲ ወይም የቢድዓ ሰው መሆኑ ግልፅ ከሆነለት እርሱን ለማሳነስ በሚል "ሰላምታዬን መልሻለሁ ተሳስቼ ነው።" ይለዋል።»