عن أبي هريرة رضي الله عنه قال: سمعت رسول الله صلى الله عليه وسلم يقول:
«حَقُّ الْمُسْلِمِ عَلَى الْمُسْلِمِ خَمْسٌ: رَدُّ السَّلَامِ، وَعِيَادَةُ الْمَرِيضِ، وَاتِّبَاعُ الْجَنَائِزِ، وَإِجَابَةُ الدَّعْوَةِ، وَتَشْمِيتُ الْعَاطِسِ».
[صحيح] - [متفق عليه]
المزيــد ...
አቢ ሁረይራ ረዲየሏሁ ዓንሁ እንዲህ ብለዋል፡ "የአሏህ መልዕክተኛ ﷺ እንዲህ ሲሉ ሰምቻለሁ፡
'አንድ ሙስሊም በሌላኛው ሙስሊም ላይ አምስት መብቶች አሉት፡ ሰላምታ መመለስ፣ ህመምተኛ መጠየቅ፣ ጀናዛን መሸኘት፣ ጥሪውን መቀበልና ባስነጠሰው ጊዜ 'የርሓሙከሏህ' ማለት ናቸው።'"
Sahih/Authentic. - [Al-Bukhari and Muslim]
ነቢዩ ﷺ አንድ ሙስሊም በሌላኛው ሙስሊም ወንድሙ ላይ ያለውን ጥቂት መብቶች ገለፁ። ከነዚህ መብቶች መካከል የመጀመሪያው ሰላምታ ለሰጠህ ሰላምታን መመለስ ነው።
ሁለተኛው መብት፡ ህመምተኛን መጠየቅና መዘየር ነው።
ሶስተኛው መብት፡ ጀናዛን ከቤቱ ወደ ሚሰገድበት ከዚያም ወደ መቃብሩ ተወስዶ እስኪቀበር ድረስ መሸኘት ነው።
አራተኛው መብት፡ ለሰርግም ይሁን ለሌላ ግብዣ ሲጠራ ጥሪውን አክብሮ ምላሽ መስጠት ነው።
አምስተኛ መብት፡ ሲያስነጥስ "ተሽሚት" ሊያደርገው ሲሆን ይሀውም አስነጥሶ "አልሓምዱሊላህ" (ትርጉሙም፡ ምስጋና ለአሏህ ይገባው) ካለ "የርሓሙከሏህ" (ትርጉሙም፡ አሏህ ይዘንልህ) ይበለው፤ ከዚያም ያስነጠሰውም መልሶ "የህዲኩሙሏሁ ወዩስሊሕ ባለኩም" (ትርጉሙም፡ አሏህ ይምራህ ጉዳይህንም ያስተካክልልህ) ይላል።