«خَيْرُ يَوْمٍ طَلَعَتْ عَلَيْهِ الشَّمْسُ يَوْمُ الْجُمُعَةِ*، فِيهِ خُلِقَ آدَمُ، وَفِيهِ أُدْخِلَ الْجَنَّةَ، وَفِيهِ أُخْرِجَ مِنْهَا، وَلَا تَقُومُ السَّاعَةُ إِلَّا فِي يَوْمِ الْجُمُعَةِ».
[صحيح] - [رواه مسلم]
المزيــد ...
ከአቡ ሁረይራ (ረዲየላሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው : ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) እንዲህ ብለዋል:
"ፀሀይ ከወጣችባቸው ቀናቶች ሁሉ በላጩ ቀን የጁመዓ ቀን ነው። በዚህ ቀን ኣደም ተፈጠረ፣ በዚሁ ቀን ጀነት ገባ፣ በዚሁ ቀን ከርሷ ወጣ፣ ሰአቲቱም በጁመዓ ቀን ካልሆነ በቀር አትከሰትም።"
ሶሒሕ ነው። - ሙስሊም ዘግበውታል።
ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ፀሀይ ከወጣችባቸው ቀናቶች ሁሉ በላጩ ቀን የጁሙዓ ቀን እንደሆነ ተናገሩ። የጁሙዓን ቀን ልዩ ከሚያደርገው ነገሮች መካከል: አላህ አደምን (ዐለይሂ ሰላም) የፈጠረው፣ ጀነት ውስጥ ያስገባው፣ ከጀነት አስወጥቶ ወደ ምድር ያወረደው በዚሁ ቀን ነው። ሰአቲቱም በጁሙዓ ቀን ካልሆነ በቀር አትከሰትም።