عن أبي هريرة رضي الله عنه قال: قال رسول الله صلى الله عليه وسلم:
«لَا تَجْعَلُوا بُيُوتَكُمْ قُبُورًا، وَلَا تَجْعَلُوا قَبْرِي عِيدًا، وَصَلُّوا عَلَيَّ؛ فَإِنَّ صَلَاتَكُمْ تَبْلُغُنِي حَيْثُ كُنْتُمْ».
[حسن] - [رواه أبو داود]
المزيــد ...
አቡ ሁረይራ ረዲየሏሁ ዓንሁ እንዲህ ብለዋል: የአሏህ መልዕክተኛ ሶለሏሁ ዓለይሂ ወስለም እንዲህ ብለዋል፡
ቤቶቻችሁን መቃብር አታድርጉ! ቀብሬንም የሚጎበኝ የበአል ስፍራ አታድርጉት! ይልቅ በኔ ላይ ሶለዋት አውርዱ! የትም ብትሆኑ ሶለዋታችሁ ትደርሰኛለችና።
Sahih/Authentic. - [Abu Dawood]
ነቢዩ ሶለላሁ ዓለይሂ ወሰለም ቤቶችን እንደ መቃብር ከሶላት የተገለሉ እና ሶላት የማይሰገድባቸው ከማድረግ እየከለከሉ ነው። እንዲሁም ልማድ አድርጎ በመያዝ የሳቸውን ቀብር ደጋግሞ መጎብኘቱንም እዚያው መሰብሰቡም ወደ ሽርክ ስለሚያደርስ ከለከሉ። ከዛ ይልቅ ወደ ቀብራቸው መመላለስ ሳያስፈልግ ቅርብም ይሁን ሩቅ እኩል ሆኖ ለሳቸው ስለሚደርሳቸው ከየትኛውም ቦታ ሆነን በሳቸው ላይ ሶለዋት እንድናወርድ አዘዙን።