+ -

عن أبي هريرة رضي الله عنه قال: قال رسول الله صلى الله عليه وسلم:
«لَا تَجْعَلُوا بُيُوتَكُمْ قُبُورًا، وَلَا تَجْعَلُوا قَبْرِي عِيدًا، وَصَلُّوا عَلَيَّ؛ فَإِنَّ صَلَاتَكُمْ تَبْلُغُنِي حَيْثُ كُنْتُمْ».

[حسن] - [رواه أبو داود] - [سنن أبي داود: 2042]
المزيــد ...

አቡ ሁረይራ ረዲየሏሁ ዐንሁ እንዲህ ብለዋል: የአሏህ መልክተኛ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና እንዲህ ብለዋል፡
"ቤቶቻችሁን መቃብር አታድርጉ! ቀብሬንም የሚጎበኝ የበአል ስፍራ አታድርጉት! ይልቅ በኔ ላይ ሶለዋት አውርዱ! የትም ብትሆኑ ሶለዋታችሁ ትደርሰኛለችና።"

[ሐሰን ነው።] - [አቡዳውድ ዘግበውታል።] - [ሱነን አቡዳውድ - 2042]

ትንታኔ

ነቢዩ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና ቤቶችን እንደ መቃብር ከሶላት የተገለሉ እና ሶላት የማይሰገድባቸው ከማድረግ እየከለከሉ ነው። እንዲሁም ልማድ አድርጎ በመያዝ የሳቸውን ቀብር ደጋግሞ መጎብኘቱንም እዚያው መሰብሰቡም ወደ ሽርክ ስለሚያደርስ ከለከሉ። ከዛ ይልቅ ወደ ቀብራቸው መመላለስ ሳያስፈልግ ቅርብም ይሁን ሩቅ እኩል ለእርሳቸው ስለሚደርሳቸው ከየትኛውም ቦታ ሆነን በሳቸው ላይ ሶለዋት እንድናወርድ አዘዙን።

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. መኖሪያ ቤቶችን አሏህን ከማምለክ የተራቆቱ ማድረግ ክልክል ነው።
  2. የነቢዩን የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና ቀብር ለመዘየር አስቦ ጉዞ መውጣት መከልከሉን እንረዳለን። የዚህም ምክንያት የትም ሆነን ሶለዋት በሳቸው ላይ እንድናወርድ ስላዘዙንና ለርሳቸው እንደሚደርሳቸውም ስለነገሩን ነው። በአምልኮ መንፈስ ጉዞ የሚወጣው ወደ መስጂድ አንነበዊ ለመሄድና እዛው ለመስገድ ከሆነ ብቻ ነው።
  3. በተለየ መልኩና ወቅትን ለይቶ የርሳቸውን ቀብር ደጋግሞ መጎብኘትን ልምድ አድርጎ መያዝ ተከልክሏል። የሌላን ሰው ቀብርም ቢሆን እንደዚሁ የተከለከለ ነው።
  4. የላቀው አሏህ ከየትኛውም ቦታና በማንኛውም ጊዜ በሳቸው ላይ ሶለዋት ማውረድን መደንገጉ ነቢዩ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና አምላካቸው ዘንድ ያላቸውን ከፍተኛ ደረጃ ያሳያል።
  5. መቃብር ዘንድ መስገድ መከልከሉ ሶሓቦች ዘንድ የፀና ጉዳይ በመሆኑ ነቢዩም የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና ባልደረቦቻቸው ቤቶቻቸውንም እንደመቃብሩ የማይሰገድበት እንዳያደርጉ ከለከሏቸው።
ትርጉም: እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ ስፔንኛ ኢንዶኔዥያኛ ኡይጙራዊ ባንጋሊኛ ፈረንሳይኛ ቱርክኛ ሩስያኛ ቦስንያኛ ሲንሃላዊ ህንድኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ቬትናማዊ ታጋሎግ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ማላያላምኛ ቴልጉ ስዋሒልኛ ታሚልኛ ቦርምኛ ታይላንድኛ ጀርመንኛ ጃፓንኛ ቡሽትኛ አሳምኛ አልባንኛ السويدية الهولندية الغوجاراتية Kyrgyzisht النيبالية Jorubisht الليتوانية الدرية الصربية الصومالية الطاجيكية Kinjaruandisht الرومانية المجرية التشيكية الموري Malagasisht الفولانية Oromisht Kannadisht الولوف البلغارية Azerisht اليونانية الأكانية الأوزبكية الأوكرانية الجورجية المقدونية
ትርጉሞችን ይመልከቱ
ተጨማሪ