عَنْ عَلِيٍّ رضي الله عنه قَالَ:
كُنْتُ رَجُلًا مَذَّاءً وَكُنْتُ أَسْتَحْيِي أَنْ أَسْأَلَ النَّبِيَّ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ لِمَكَانِ ابْنَتِهِ فَأَمَرْتُ الْمِقْدَادَ بْنَ الْأَسْوَدِ فَسَأَلَهُ فَقَالَ: «يَغْسِلُ ذَكَرَهُ وَيَتَوَضَّأُ».
وَلِلبُخَاريِّ: فَقَالَ: «تَوَضَّأْ وَاغْسِلْ ذَكَرَكَ».
[صحيح] - [متفق عليه]
المزيــد ...
ከዐሊ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው እንዲህ አሉ:
"መዚይ (ስሜት በሚቀሰቀስ ወቅት የሚወጣ ፈሳሽ ነው።) የሚበዛብኝ ሰው ነበርኩ። ልጃቸው እኔ ዘንድ በመሆኗ ነቢዩን (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) (ስለብይኑ) መጠየቅ አፈርኩና ሚቅዳድ ቢን አስወድን እንዲጠይቃቸው አዘዝኩት፤ ጠየቃቸው። እርሳቸውም 'ብልቱን ይታጠብና ዉዱእ ያድርግ።' አሉ።" በቡኻሪ ዘገባ ደሞ "ዉዱእ አድርግ፤ ብልትህንም እጠብ።"
Sahih/Authentic. - [Al-Bukhari]
ዐሊይ ቢን አቢ ጧሊብ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና መዚይ (ነጭ፣ ቀጭን፣ የሚዝለገለግ፣ ስሜት በሚቀሰቀስ ወቅት ወይም ከግንኙነት በፊት የሚወጣ ፈሳሽ ነው።) ብዙ ጊዜ ይወጣቸው እንደነበር ተናገሩ። መውጣቱን ተከትሎ እንዴት ማድረግ እንዳለባቸውም አያውቁም። የነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ልጅ ፋጢማ ባለቤት ስለሆኑ ነቢዩን (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) መጠየቅ አፈሩ። ሚቅዳድ ቢን አስወድ ነቢዩን (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ስለዚህ ጉዳይ እንዲጠይቅላቸው አድርገው ላኩት። ነቢዩም (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ብልቱን አጥቦ ዉዱእ ማድረግ እንደሚገባው በመንገር መልስ ሰጡት።