+ -

عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ رضي الله عنه قَالَ: إِنَّ رَسُولَ اللهِ صلى الله عليه وسلم قَالَ:
«إِذَا شَرِبَ الْكَلْبُ فِي إِنَاءِ أَحَدِكُمْ فَلْيَغْسِلْهُ سَبْعًا». ولمسلم: « أولاهُنَّ بالتُراب».

[صحيح] - [متفق عليه] - [صحيح البخاري: 172]
المزيــد ...

ከአቡ ሁረይራ (ረዲየላሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው እንዲህ አሉ: «የአላህ መልክተኛ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) እንዲህ ብለዋል:
"ውሻ ከአንዳችሁ እቃ የጠጣ ጊዜ (እቃውን) ሰባት ጊዜ ይጠበው።"»

[ሶሒሕ ነው።] - [ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል።] - [ሶሒሕ አልቡኻሪ - 172]

ትንታኔ

ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ውሻ እቃ ውስጥ ምላሱን ያስገባ ጊዜ እቃው ሰባት ጊዜ እንዲታጠብ አዘዙ። ከነዚህ ሰባት ትጥበቶች የመጀመሪያውን በአፈር ቀላቅሎ ይጠበው ይህም ከዛ በኋላ ውሃ በተደጋጋሚ እንዲፈስበት ነው። በዚህም ከነጃሳውና ከጉዳቶቹ የተሟላ መፅዳት ይገኛል።

ትርጉም: እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ ስፔንኛ ኢንዶኔዥያኛ ኡይጙራዊ ፈረንሳይኛ ቱርክኛ ሩስያኛ ቦስንያኛ ሲንሃላዊ ህንድኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ቬትናማዊ ታጋሎግ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ማላያላምኛ ስዋሒልኛ ታይላንድኛ ቡሽትኛ አሳምኛ السويدية الهولندية الغوجاراتية النيبالية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. የውሻ ምራቅ ከባድ ነጃሳ ነው።
  2. ውሻ እቃ ውስጥ ምላሱን በመንከር መጠጣቱ እቃውንም ውስጡ ያለውን ውሃም ይነጅሰዋል።
  3. በአፈር ማፅዳትና በውሃም ሰባት ጊዜ መደጋገም የውሻ ሽንት፣ ሰገራና ሌሎችም ውሻ ያቆሸሻቸው ነገሮች የሚፀዱበት አፀዳድ ሳይሆን በአፉ የነካ ጊዜ ብቻ የሚፈፀም የአፀዳድ አይነት ነው።
  4. እቃ በአፈር የሚፀዳበት የአፀዳድ አፈፃፀም: እቃ ውስጥ ውሃ ያደርግና አፈር ይጨምርበታል። ቀጥሎ በዚህ ከአፈር ጋር በተቀላቀለ ውሃ የተነጀሰውን እቃ ያጥባል።
  5. የሐዲሡ ግልፅ መልዕክት ሸሪዓ ቤታችን እንድናደርጋቸው የፈቀዳቸውን ውሻዎችንም ሳይቀር የአደን፣ የጥበቃ፣ ለአዝርእትና ከብቶች ጥበቃ የምናሳድጋቸውን ውሻዎች ይመስል ሁሉንም ውሻዎች ያጠቃልላል።
  6. ሳሙናና እንዶድ የአፈርን ቦታ አይተኩም። ይህም ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ለይተው አፈር ብለው በግልፅ ስላስቀመጡ ነው።