عن جندب رضي الله عنه قال:
سمعت النبي صلى الله عليه وسلم قبل أن يموت بخمسٍ وهو يقول: «إني أبرأ إلى الله أن يكون لي منكم خليلٌ، فإن الله تعالى قد اتخذني خليلًا، كما اتخذ إبراهيم خليلًا، ولو كنت متخذًا من أمتي خليلًا لاتخذت أبا بكر خليلًا، ألا وإن من كان قبلكم كانوا يتخذون قبور أنبيائهم وصالحيهم مساجد، ألا فلا تتخذوا القبور مساجد، إني أنهاكم عن ذلك».

[صحيح] - [رواه مسلم]
المزيــد ...

ጁንዱብ ረዲየሏሁ ዓንሁ እንዲህ ብሏል፡
"ነብዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ከመሞታቸው አምስት (ሌሊቶች) በፊት እንዲህ ሲሉ ሰምቻቸዋለሁ፡- ' እኔ ከናንተ መካከል ፍፁም ወዳጅ ከመያዝ ወደ አላህ እጥራራለሁ። ምክንያቱም የላቀው አሏህ ኢብራሂምን ፍፁም ወዳጅ አድርጎ እንደያዘው ሁሉ እኔንም ፍፁም ወዳጅ አድርጎ ይዞኛልና። ከኡመቴ ፍፁም ወዳጅ አድርጌ የምይዝ ብሆን ኖሮ አቡበከርን ነበር ፍፁም ወዳጅ አድርጌ የምይዘው። አዋጅ! እነዚያ ከናንተ በፊት የነበሩት የነብያቶቻቸውንና የፃድቃኖቻቸውን መቃብር መስገጃ ስፍራ አድርገው ይይዙ ነበር። አዋጅ! መቃብርን መስገጃ ስፍራ አድርጋችሁ አትያዙ! እኔ እየከለከልኳችሁ ነው።'"

Sahih/Authentic. - [Muslim]

ትንታኔ

ነቢዩ ሶለሏሁ ዓለይሂ ወሰለም በአላህ ዘንድ ያላቸው ደረጃ አሳወቁ፤ ልክ እንደ ኢብራሂም ዐለይሂ ሰላም እሳቸውም ላእላይ እርከን የደረሰ ውዴታ መጎናፀፋቸውንም ተናገሩ። ከአሏህ ውጭ ፍፁም ወዳጅ ሊኖራቸው እንደማይችል ገለፁ። ምክንያቱም ልባቸው በአላህ ውዴታ፣ ማላቅና ማወቅ ተሞልቷልና ከአላህ ውጪ ለሳቸው ሌላ ፍፁም ወዳጅ ሊኖራቸው አይችልም። ከፍጡራን ፍፁም ወዳጅ የሚይዙ ቢሆኑ ኖሮ ያ ሰው አቡበከር አስሲዲቅ አላህ መልካም ስራውን ይውደድለትና ይሆን ነበር። ከዚያም አይሁዶችና ክርስቲያኖች የነቢያቶቻቸውና የፃድቃኖቻቸው መቃብር ከአላህ ውጪ ወደምትመለክ ጣኦታዊ የአምልኮ ስፍራ እስክትለወጥ እንዲሁም መስጂድና ምኩራብ መቃብሮቻቸው ላይ በመገንባት የፈፀሙትን ልክ ያለፈ የውዴታ ድንበር ማለፍ አስጠነቀቁ። አስከትለውም ኡመታቸውም የነሱን አይነት ድርጊት እንዳይፈፅሙ ከለከሉ።

ትርጉም: እንግሊዝኛ ፈረንሳይኛ ስፔንኛ ቱርክኛ የኡርዱ ቋንቋ ኢንዶኔዥያኛ ቦስንያኛ ሩስያኛ ባንጋሊኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ታጋሎግ ህንድኛ ቬትናማዊ ሲንሃላዊ ኡይጙራዊ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ማላያላምኛ ቴልጉ ስዋሒልኛ ታሚልኛ ቦርምኛ ታይላንድኛ ጀርመንኛ ጃፓንኛ ቡሽትኛ አሳምኛ አልባንኛ السويدية الهولندية الغوجاراتية الدرية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. አቡበክር ሲዲቅ ረዲየሏሁ ዓንሁ ያለውን በላጭነት፤ ከሶሓቦችም ሁሉ በላጩ እርሱ መሆኑንና ከረሱል ዓለይሂ ሶላቱ ወሰላም በኋላ በሳቸው የመሪነት ቦታ ለመተካት ይበልጥ የተገባውም እርሱ መሆኑን፤
  2. በመቃብር ላይ መስገጃ መገንባት ያለፉት ህዝቦች ከሚፈፅሟቸው ውግዝ ተግባራት መካከል መሆኑ፤
  3. ወደ ሽርክ ሊያደርስ ስለሚችል መቃብርን የአምልኮ ስፍራ አድርጎ መያዝ፣ በውስጧም ሆነ ወደሷ ዞሮ መስገድ፣ ወይም በላያቸው ላይ መስገጃ ወይም ጉልላት መስራት ክልክል መሆኑ፤
  4. ወደ ሽርክ ሊያደርስ ስለሚችል በፃድቃን ላይ ድንበር ከማለፍ መጠንቀቅን፤
  5. ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ከመሞታቸው አምስት ቀናት ቀደም ብለው ማስጠንቀቃቸው ያስጠነቀቁት ጉዳይ ያለውን አሳሳቢነት እንደሚያሳይ እንረዳለን።