عن جندب رضي الله عنه قال:
سَمِعْتُ النَّبِيَّ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ قَبْلَ أَنْ يَمُوتَ بِخَمْسٍ وَهُوَ يَقُولُ «إِنِّي أَبْرَأُ إِلَى اللهِ أَنْ يَكُونَ لِي مِنْكُمْ خَلِيلٌ فَإِنَّ اللهَ تَعَالَى قَدِ اتَّخَذَنِي خَلِيلًا كَمَا اتَّخَذَ إِبْرَاهِيمَ خَلِيلًا، وَلَوْ كُنْتُ مُتَّخِذًا مِنْ أُمَّتِي خَلِيلًا لَاتَّخَذْتُ أَبَا بَكْرٍ خَلِيلًا! أَلَا وَإِنَّ مَنْ كَانَ قَبْلَكُمْ كَانُوا يَتَّخِذُونَ قُبُورَ أَنْبِيَائِهِمْ وَصَالِحِيهِمْ مَسَاجِدَ، أَلَا فَلَا تَتَّخِذُوا الْقُبُورَ مَسَاجِدَ! إِنِّي أَنْهَاكُمْ عَنْ ذَلِكَ».
[صحيح] - [رواه مسلم] - [صحيح مسلم: 532]
المزيــد ...
ከጁንዱብ ረዲየሏሁ ዐንሁ እንደተላለፈው እንዲህ ብለዋል፡
"ነብዩ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ከመሞታቸው አምስት (ሌሊቶች) በፊት እንዲህ ሲሉ ሰምቻቸዋለሁ፡- ' እኔ ከናንተ መካከል ፍፁም ወዳጅ ከመያዝ ወደ አላህ እጥራራለሁ። ምክንያቱም የላቀው አሏህ ኢብራሂምን ፍፁም ወዳጅ አድርጎ እንደያዘው ሁሉ እኔንም ፍፁም ወዳጅ አድርጎ ይዞኛልና። ከኡመቴ መካከል ፍፁም ወዳጅ አድርጌ የምይዝ ብሆን ኖሮ አቡበከርን ነበር ፍፁም ወዳጅ አድርጌ የምይዘው። አዋጅ! እነዚያ ከናንተ በፊት የነበሩት የነብያቶቻቸውንና የፃድቃኖቻቸውን መቃብር መስገጃ ስፍራ አድርገው ይይዙ ነበር። አዋጅ! መቃብርን መስገጃ ስፍራ አድርጋችሁ አትያዙ! እኔ እየከለከልኳችሁ ነው።'"
[ሶሒሕ ነው።] - [ሙስሊም ዘግበውታል።] - [ሶሒሕ ሙስሊም - 532]
ነቢዩ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና በአላህ ዘንድ ያላቸውን ደረጃ አሳወቁ፤ ልክ እንደ ኢብራሂም ዐለይሂ ሰላም እሳቸውም ላእላይ እርከን የደረሰ ውዴታ መጎናፀፋቸውንም ተናገሩ። ልባቸው በአላህ ውዴታ፣ ማላቅና ማወቅ ስለተሞላ ከአሏህ ውጭ ፍፁም ወዳጅ ሊኖራቸው እንደማይችልም ገለፁ። ከፍጡራን መካከል ፍፁም ወዳጅ የሚይዙ ቢሆኑ ኖሮ ያ ሰው አቡበከር አስሲዲቅ አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸውና ይሆን እንደነበረም ተናገሩ። ከዚያም አይሁዶችና ክርስቲያኖች የነቢያቶቻቸውንና የፃድቃኖቻቸውን መቃብር ከአላህ ውጪ ወደምትመለክ ጣኦታዊ የአምልኮ ስፍራ በመለወጥ እንዲሁም የፃድቃኖችና ነቢያቶች መቃብር ላይ መስገጃና ቤተ መቅደሶችን በመገንባት የፈፀሙትን ልክ ያለፈ የውዴታ ድንበር ከማለፍ አስጠነቀቁ። አስከትለውም ኡመታቸውም የነሱን አይነት ድርጊት እንዳይፈፅሙ ከለከሉ።