عن أبي صِرْمة رضي الله عنه أن رسول الله صلى الله عليه وسلم قال:
«مَنْ ضَارَّ ضَارَّ اللهُ بِهِ، وَمَنْ شَاقَّ شَقَّ اللهُ عَلَيْهِ».

[حسن] - [رواه أبو داود والترمذي وابن ماجه وأحمد] - [سنن الترمذي: 1940]
المزيــد ...

ከአቡ ሲርመህ -አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸውና- እንደተላለፈው የአላህ መልክተኛ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም እንዲህ አሉ:
"የጎዳ ሰው አላህም ይጎዳዋል ፤ ያስጨነቀንም አላህም ያስጨንቀዋል።"

[ሐሰን ነው።] - [አቡዳውድ፣ ቲርሚዚ፣ ኢብኑማጀህና አሕመድ ዘግበውታል።] - [ሱነን ቲርሚዚ - 1940]

ትንታኔ

ነቢዩ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም በነፍሱም ይሁን በገንዘቡም ይሁን በቤተሰቡም ይሁን በማንኛውም ጉዳዩ ላይ ሙስሊም ላይ ጉዳትና ችግርን ከማድረግ አስጠነቀቁ። ይህንንም ለፈፀመ አላህም በሰራው አምሳያ እንደሚመነዳውና እንደሚቀጣው ገለፁ።

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. ሙስሊምን መጉዳትና ማስጨነቅ መከልከሉን ፤
  2. አላህ ለባሮቹ የሚበቀል መሆኑን እንረዳለን።
ትርጉሞችን ይመልከቱ
ቋንቋ: እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ ስፔንኛ ተጨማሪ (67)