+ -

عن أبي هريرة رضي الله عنه أَن النبيَّ صَلّى اللهُ عَلَيْهِ وسَلَّم قَالَ:
«الرَّجُلُ عَلَى دِينِ خَلِيلِهِ، فَلْيَنْظُر أَحَدُكُم مَنْ يُخَالِل».

[حسن] - [رواه أبو داود والترمذي وأحمد] - [سنن أبي داود: 4833]
المزيــد ...

ከአቡ ሁረይራ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው : ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) እንዲህ ብለዋል:
"ሰውዬው በጓደኛው ሃይማኖት ላይ ነው። አንዳችሁ የሚጎዳኘውን ሰው ይመልከት።"

[ሐሰን ነው።] - [አቡዳውድ፣ ቲርሚዚና አሕመድ ዘግበውታል።] - [ሱነን አቡዳውድ - 4833]

ትንታኔ

ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) የሰው ልጅ ፍፁም ጓደኛውንና ባልደረባውን በልማዱና ኑሮው እንደሚመሳሰል፤ ጓደኝነትም በስነምግባር፣ በባህሪና የኑሮ ዘይቤ ላይ ተፅዕኖ እንደሚያሳድር ገለፁ። ለዚህም ጓደኛ አመራረጣችንን እንድናሳምር ጠቆሙ። ምክንያቱም ጥሩ ጓደኛ ወደ ኢማን፣ ቅናቻና መልካም ነገር ይጠቁማል። ለባልደረባውም አጋዥ ይሆናልና።

ትርጉም: እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ ስፔንኛ ኢንዶኔዥያኛ ባንጋሊኛ ፈረንሳይኛ ቱርክኛ ሩስያኛ ቦስንያኛ ሲንሃላዊ ህንድኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ቬትናማዊ ታጋሎግ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ማላያላምኛ ስዋሒልኛ ታይላንድኛ ቡሽትኛ አሳምኛ السويدية الهولندية الغوجاراتية النيبالية الصومالية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. መልካሞችን በመወዳጀትና በመምረጥ መታዘዙን፤ መጥፎዎችን መወዳጀት ደግሞ መከልከሉን እንረዳለን።
  2. ከዘመድ ይልቅ ጓደኛን ብቻ ለይተው መጥቀሳቸው ጓደኛ አንተ ራስህ ነህ የምትመርጠው ስለሆነ፤ ወንድምና ቅርብ ዘመድ ግን አንተ ምንም ምርጫ ስለሌለህ ነው።
  3. ጓደኛን መያዝ የግድ ከማስተዋል በኋላ የመጣ መሆን አለበት።
  4. አንድ ሰው አማኞችን በመወዳጀት ዲኑን እንደሚያጠነክርና አመፀኞችን በመወዳጀት ደግሞ እንደሚያደክመው እንረዳለን።