عَنْ مَطَرِ بْنِ عُكَامِسٍ رضي الله عنه قَالَ: قَالَ رَسُولُ اللهِ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ:
«إِذَا قَضَى اللَّهُ لِعَبْدٍ أَنْ يَمُوتَ بِأَرْضٍ جَعَلَ لَهُ إِلَيْهَا حَاجَةً».

[صحيح] - [رواه الترمذي] - [سنن الترمذي: 2146]
المزيــد ...

መጠር ቢን ዑካሚስ -አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸውና- እንዲህ አሉ፦ የአላህ መልክተኛ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን እንዲህ ብለዋል፦
"አላህ አንድ ባሪያ በአንድ ቦታ እንዲሞት የወሰነ ጊዜ ወደዚያ ስፍራ የሚሄድበትን ምክንያት ያደርግለታል።"

[ሶሒሕ ነው።] - [ቲርሚዚ ዘግበውታል።] - [ሱነን ቲርሚዚ - 2146]

ማብራሪያ

ነቢዩ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን፦ አንድ ባሪያ እሱ በማይኖርበት አንድ ስፍራ እንዲሞት አላህ የወሰነና የፈረደ ጊዜ ወደዛ ስፍራ የሚሄድበት ምክንያት (ጉዳይ) ያደርግበትና ይሄዳል። እዛም ስፍራ ላይ ነፍሱ ትያዛለች። በማለት ተናገሩ።

ከሐዲሡ የሚቀሰሙ ቁምነገሮች

  1. ይህ ሐዲሥ {ማንኛይቱ ነፍስም በየትኛው ምድር እንደምትሞት አታውቅም።} ለሚለው የአላህ ንግግር ማረጋገጫ ነው።
ትርጉሞችን አሳይ
ቋንቋ: الإنجليزية الأوردية الإسبانية ተጨማሪ (68)
ተጨማሪ