عن أبي هريرة رضي الله عنه قال: قال رسول الله صلى الله عليه وسلم:
«مَنْ كَذَبَ عَلَيَّ مُتَعَمِّدًا فَلْيَتَبَوَّأْ مَقْعَدَهُ مِنَ النَّارِ».

[صحيح] - [متفق عليه]
المزيــد ...

ከአቡ ሁረይራ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው እንዲህ አሉ: "የአላህ መልክተኛ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) እንዲህ ብለዋል:
"ሆነ ብሎ በኔ ላይ የዋሸ ሰው ከእሳት የሆነ መቀመጫውን ያዘጋጅ።"

Sahih/Authentic. - [Al-Bukhari and Muslim]

ትንታኔ

ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ሆን ብሎ ንግግርን ወይም ድርጊትን ወደርሳቸው አስጠግቶ በርሳቸው ላይ የዋሸ ሰው በመጨረሻው ዓለም በርሳቸው ላይ ለመዋሸቱ ምንዳ የእሳት መቀመጫ እንዳለው ገለፁ።

ትርጉም: እንግሊዝኛ ፈረንሳይኛ የኡርዱ ቋንቋ ኢንዶኔዥያኛ ቦስንያኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ህንድኛ ሲንሃላዊ ኡይጙራዊ ኩርዳዊ ሃውሳ ማላያላምኛ ስዋሒልኛ ታሚልኛ ቦርምኛ ታይላንድኛ ቡሽትኛ አሳምኛ السويدية الهولندية الغوجاراتية الدرية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. በነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ላይ አውቆና ሆን ብሎ መዋሸት እሳት ለመግባት ምክንያት እንደሆነ እንረዳለን።
  2. በነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ላይ መዋሸትን ተከትሎ ከሚመጣው ዱንያዊና ሃይማኖታዊ ብልሽት ከባድነት አንፃር እርሳቸው ላይ መዋሸት በሌሎች ሰዎች ላይ እንደመዋሸት እንዳልሆነ እንረዳለን።
  3. ሐዲሦች በትክክል ከነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) መነገራቸውን ሳናረጋግግጥ በፊት ማሰራጨት መከልከሉን እንረዳለን።