عَنْ ‌أَبِي هُرَيْرَةَ رضي الله عنه قَالَ:
قَالَ رَسُولُ اللهِ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ لِعَمِّهِ: «قُلْ: لَا إِلَهَ إِلَّا اللهُ، أَشْهَدُ لَكَ بِهَا يَوْمَ الْقِيَامَةِ»، قَالَ: لَوْلَا أَنْ تُعَيِّرَنِي قُرَيْشٌ، يَقُولُونَ: إِنَّمَا حَمَلَهُ عَلَى ذَلِكَ الْجَزَعُ لَأَقْرَرْتُ بِهَا عَيْنَكَ. فَأَنْزَلَ اللهُ: {إِنَّكَ لا تَهْدِي مَنْ أَحْبَبْتَ وَلَكِنَّ اللهَ يَهْدِي مَنْ يَشَاءُ } [القصص: 56].

[صحيح] - [رواه مسلم]
المزيــد ...

አቡ ሁረይራ -አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና- እንዲህ ብለዋል፦
የአላህ መልክተኛ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን ለአጎታቸው እንዲህ አሏቸው፦ " ላ ኢላሀ ኢለላህ በል የትንሳኤ ቀን ላንተ በርሱ እመሰክርልሀለሁ" አቡ ጣሊብም "የቁረይሾች ማነወር ባልነበር "ለመስለም ያነሳሳው የሞት ፍራቻ ነው" ይላሉ ብዬ ባልሰጋ (እሰልም ነበር)" (ይህ ስጋት ባልነበር) ላ ኢላሀ ኢለላህ በማለት ደስታን አሰርፅልህ ነበር።" አላቸው። አላህም ይህቺን አንቀፅ አወረደ {አንተ የወደድከውን ሰው ፈፅሞ አታቀናም። ግን አላህ የሚሻውን ሰው ያቀናል እርሱም ቅኖቹን አዋቂ ነው።} [አልቀሶስ: 56]

Sahih/Authentic. - [Muslim]

ትንታኔ

ነቢዩ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን አጎታቸው አቡ ጣሊብ ጣእረ ሞት ላይ ሳሉ ላኢላሀ ኢለላህን እንዲናገር ፈለጉ። ይህም የትንሳኤ ቀን በሷ ምክንያት ሊያማልዱትና በእስልምናው ሊመሰክሩለት ብለው ነው። እርሳቸው ግን ቁረይሾች እንዳይሰድቧቸው ፈርተውና "እርሱ የሰለመው ሞትና ደካማነትን በመፍራቱ ምክንያት ነው!" እንዳይባሉ በመስጋት የምስክርነት ቃሏን መናገር እምቢ አሉ። ለነቢዩም የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን "ይህ ስጋቴ ባልነበር የምስክር ቃሏን በመናገር በልብዎ ውስጥ ደስታን አስገባም ነበር እስኪደሰቱ ድረስም ምኞቶን አሳካ ነበር" አሏቸው። አላህም የፈለገውን ሰው እርሱ ብቻ እንጂ ነቢዩም የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን ኢስላምን በሰው ቀልብ ውስጥ በማስረፅ መምራት እንደማይችሉ የሚጠቁም አንቀፅ አወረደ። ነቢዩ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን ፍጡራንን ወደ ቀጥተኛው መንገድ በመጠቆም ፣ በማብራራት፣ በማቅናትና በመጣራት ነው የሚመሩት።

ትርጉም: እንግሊዝኛ ፈረንሳይኛ ስፔንኛ ቱርክኛ የኡርዱ ቋንቋ ኢንዶኔዥያኛ ቦስንያኛ ባንጋሊኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ህንድኛ ቬትናማዊ ሲንሃላዊ ኡይጙራዊ ኩርዳዊ ሃውሳ ማላያላምኛ ቴልጉ ስዋሒልኛ ታሚልኛ ቦርምኛ ታይላንድኛ ቡሽትኛ አሳምኛ አልባንኛ السويدية الهولندية الغوجاراتية الدرية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. የሰዎችን ወሬ በመፍራት ሐቅ እንደማትተው!
  2. ነቢዩ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን የመጠቆምና የማቅናት መምራት እንጂ የሚችሉት ልብ ውስጥ የማስረፅ መምራት እንደማይችሉ፤
  3. ወደ ኢስላም ለመጥራት ብሎ የታመመን ከሀዲ መዘየር በኢስላም የተደነገገ መሆኑን፤
  4. ነቢዩ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን በማንኛውም ሁኔታዎች ወደ አላህ በመጥራት ላይ የነበራቸውን ጉጉት ተረድተናል።