عَنْ طَاوُسٍ أَنَّهُ قَالَ: أَدْرَكْتُ نَاسًا مِنْ أَصْحَابِ رَسُولِ اللهِ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ، يَقُولُونَ كُلُّ شَيْءٍ بِقَدَرٍ، قَالَ: وَسَمِعْتُ عَبْدَ اللهِ بْنَ عُمَرَ رضي الله عنهما يَقُولُ: قَالَ رَسُولُ اللهِ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ:
«كُلُّ شَيْءٍ بِقَدَرٍ، حَتَّى الْعَجْزِ وَالْكَيْسِ، أَوِ الْكَيْسِ وَالْعَجْزِ».

[صحيح] - [رواه مسلم]
المزيــد ...

ጣዉስ እንዲህ አሉ፦ "የአላህ መልክተኛ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን ባለደረቦች የሆኑ ሰዎችን አግኝቻለሁ። "ሁሉም ነገር በአላህ ውሳኔ ነው"ይሉም ነበር። ጣዉስ እንዲህም አሉ፦ " ዐብደላህ ቢን ዑመርን -አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸውና - እንዲህ ሲሉ ሰምቻቸዋለሁ፦ የአላህ መልክተኛ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን እንዲህ ብለዋል፦
"ስንፍናና ጮሌነት ወይም ጮሌነትና ስንፍና ሳይቀር ሁሉ ነገር በአላህ ውሳኔ ነው።"

Sahih/Authentic. - [Muslim]

ትንታኔ

ነቢዩ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን ሁሉም ነገር በአላህ ውሳኔ መሆኑን ገለፁ። ስንፍና ሳይቀር ተወስኗል: እሱም: - ዱንያዊና አኺራዊ ከሆኑ ጉዳዮች መስራት ግድ የሆነበትን ነገር መተው፣ ሳይሰሩ መገኘት ፣ ከወቅቱ ማዘግየት ነው። ጮሌነት ሳይቀር ተወስኗል: እሱም:- ዱንያዊና አኺራዊ ጉዳዮችን ለመስራት መነቃቃትና ብልህ መሆን ማለት ነው። የላቀውና የተከበረው አላህ ስንፍናና ጮሌነትን ሳይቀር ሁሉንም ነገር ወስኗል። በዚህ ዓለም የአላህ ዕውቀትና ፍላጎት የቀደመው ጉዳይ ካልሆነ በስተቀር አይከሰትም።

ትርጉም: እንግሊዝኛ ፈረንሳይኛ ስፔንኛ ቱርክኛ የኡርዱ ቋንቋ ኢንዶኔዥያኛ ቦስንያኛ ባንጋሊኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ህንድኛ ቬትናማዊ ሲንሃላዊ ኡይጙራዊ ኩርዳዊ ሃውሳ ማላያላምኛ ቴልጉ ስዋሒልኛ ታሚልኛ ቦርምኛ ታይላንድኛ ቡሽትኛ አሳምኛ አልባንኛ السويدية الهولندية الغوجاراتية الدرية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. በአላህ ውሳኔ (ቀደር) ጉዳይ የሰሐቦች -አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና- እምነት መገለፁ።
  2. ስንፍናና ንቁነት ሳይቀር ሁሉም ነገር የሚከሰተው በአላህ ውሳኔ መሆኑን፤
  3. የአላህ መልክተኛን የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን ሐዲሥ በማስተላለፉ ረገድ የሰሐቦች -አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና- ጥንቃቄና ማረጋገጥ፤
  4. በመልካሙም ሆነ በመጥፎው ሁሉም ጉዳይ በአላህ ውሳኔ መሆኑን ማመንን ተረድተናል።