+ -

عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ رضي الله عنه قَالَ: قَالَ رَسُولُ اللهِ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ:
«مَا يَزَالُ البَلاَءُ بِالمُؤْمِنِ وَالمُؤْمِنَةِ فِي نَفْسِهِ وَوَلَدِهِ وَمَالِهِ حَتَّى يَلْقَى اللَّهَ وَمَا عَلَيْهِ خَطِيئَةٌ».

[حسن] - [رواه الترمذي وأحمد] - [سنن الترمذي: 2399]
المزيــد ...

ከአቡ ሁረይራ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) እንደተላለፈው እንዲህ ብለዋል፦ «የአሏህ መልዕክተኛ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) እንዲህ ብለዋል፡
"አማኝ የሆነ ወንድና ሴት በርሱ ላይ ምንም ወንጀል የሌለበት ሆኖ አላህን እስኪገናኝ ድረስ በነፍሱ፣ በልጁና በገንዘቡ ላይ መከራ ከመከሰት አይወገድም።"»

[ሐሰን ነው።] - [ቲርሚዚና አሕመድ ዘግበውታል።] - [ሱነን ቲርሚዚ - 2399]

ትንታኔ

ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) አማኝ የሆነ ወንድና ሴት ባሪያ ከፈፀማቸው ሁሉም ወንጀሎችና ኃጢዐቶች የፀዳ ሆኖ አላህን እስኪገናኝ ድረስና በነዚህ መከራዎች ሁሉንም ወንጀሎቹን አላህ እስኪምረው ድረስ በነፍሱ (በጤናውና በአካሉ)፣ በልጆቹ (በህመም ወይም ሞት ወይም በነርሱ በመበደል ወይም ከዚህ ውጪ ባሉ በልጆች ሳቢያ በሚደርሱ መከራዎች)፣ በገንዘቡ (በመደኽየት፣ ንግዱን በመክሰር፣ በመሰረቅ፣ በኑሮ መወደድ፣ በሲሳይ መጥበብ) የሚያጋጥመው መከራና ፈተና አይላቀቀውም።

ትርጉም: እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ ስፔንኛ ኢንዶኔዥያኛ ባንጋሊኛ ፈረንሳይኛ ቱርክኛ ሩስያኛ ቦስንያኛ ሲንሃላዊ ህንድኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ቬትናማዊ ታጋሎግ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ማላያላምኛ ስዋሒልኛ ታይላንድኛ ቡሽትኛ አሳምኛ السويدية الهولندية الغوجاراتية النيبالية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. አላህ ለአማኝ ባሮቹ ካለው እዝነት በዱንያ መከራዎችና ፈተናዎች አማካይነት በዱንያ ላይ እያሉ ወንጀሎቻቸውን ከነርሱ መማሩ ነው።
  2. መከራ ብቻውን ወንጀልን ያስምራል ለዚህም አምኖ መገኘት ቅድመ መስፈርቱ ነው። አንድ ባሪያ ከታገሰና ካልተማረረ ይመነዳል።
  3. በሚወደውም፣ በሚጠላውም በሁሉም ጉዳዮች በመታገስ ላይ መነሳሳቱን እንረዳለን። የአላህን ምንዳ በመፈለግና ቅጣቱን በመፍራት አላህ ግዴታ ያደረገበትን በአግባቡ በመፈፀምና አላህ ክልክል ያደረገበትን ነገር በመራቅ ላይ መታገስ ይገባዋል።
  4. ሐዲሡ ውስጥ "በአማኝ ወንድና ሴት ላይ" የሚለው ንግግር: አማኝ ሴት የሚለው መጨመሩ ለሴቶች ተጨማሪ አፅንዖት ለመስጠት ነው። ያለበለዚያ "አማኝ" ብቻ ቢሉም በዚህ ውስጥ ሴት ትጠቃለል ነበር። ጉዳዩ በወንድ ላይ ብቻ የተገደበ አይደለምና። መከራ በሴት ላይም ቢከሰት ልክ እንደወንዱ ወንጀሏና ኃጢአቷ በመማር ተመሳሳይ ምንዳ ቃል ተገብቶላታል።**
  5. አንድ ባሪያ በተደጋጋሚ በሚያጋጥሙት ህመሞች ላይ ከሚያቀሉለት ነገሮች አንዱ መከራውን ተከትለው የሚያገኛቸው ትሩፋቶች ናቸው።
ተጨማሪ