+ -

عَن سَهْلِ بْنِ حُنَيْفٍ رضي الله عنه أَنَّ النَّبِيَّ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ قَالَ:
«مَنْ سَأَلَ اللهَ الشَّهَادَةَ بِصِدْقٍ بَلَّغَهُ اللهُ مَنَازِلَ الشُّهَدَاءِ، وَإِنْ مَاتَ عَلَى فِرَاشِهِ».

[صحيح] - [رواه مسلم] - [صحيح مسلم: 1909]
المزيــد ...

ከሰህል ቢን ሑነይፍ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) እንዲህ ብለዋል:
"የእውነት ሰማእትነትን እንዲሰጠው አላህን የጠየቀ ሰው ፍራሹ ላይ ቢሞት እንኳ አላህ የሰማእታትን ደረጃ ያደርሰዋል።"

[ሶሒሕ ነው።] - [ሙስሊም ዘግበውታል።] - [ሶሒሕ ሙስሊም - 1909]

ትንታኔ

ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) በአላህ መንገድ ሰማእት መሆንንና መገደልን የፈለገ፣ በዚህ ፍላጎቱም ለአላህ አጥርቶና እውነተኛ ሆኖ ከሆነ የጠየቀው ጂሀድ ሳያደርግ ፍራሽ ላይ ቢሞት እንኳ አላህ በእውነተኛ ኒያው የሰማእታትን ደረጃ እንደሚሰጠው ተናገሩ።

ትርጉም: እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ ስፔንኛ ኢንዶኔዥያኛ ባንጋሊኛ ፈረንሳይኛ ቱርክኛ ሩስያኛ ቦስንያኛ ሲንሃላዊ ህንድኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ቬትናማዊ ታጋሎግ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ማላያላምኛ ስዋሒልኛ ታይላንድኛ ቡሽትኛ አሳምኛ السويدية الهولندية الغوجاراتية النيبالية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. የተፈለገውን ሥራ ባይሰራ እንኳ የሚቻለውን ከመስራት ጋር እውነተኛ ኒያ መነየት የተፈለገው ምንዳና አጅር ላይ ለመድረስ ሰበብ እንደሚሆነው እንረዳለን።
  2. ጂሀድ ማድረግና በአላህ መንገድ ሰማእት መሆን በመፈለግ ላይ መነሳሳቱን እንረዳለን።
  3. አላህ ይህን ኡማ ማላቁን እንረዳለን። ይህ ኡማ በትንሽ ስራ ጀነት ውስጥ ከፍተኛ ደረጃን እንዲያገኝ ታድሏልና።