عَنِ ابْنِ مَسْعُودٍ رضي الله عنه عَنِ النَّبِيِّ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ قَالَ:
«سَتَكُونُ أَثَرَةٌ وَأُمُورٌ تُنْكِرُونَهَا» قَالُوا: يَا رَسُولَ اللَّهِ فَمَا تَأْمُرُنَا؟ قَالَ: «تُؤَدُّونَ الحَقَّ الَّذِي عَلَيْكُمْ، وَتَسْأَلُونَ اللَّهَ الَّذِي لَكُمْ».

[صحيح] - [متفق عليه]
المزيــد ...

ከኢብኑ መስዑድ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) እንዲህ ብለዋል፦
"ለወደፊት የምታወግዟቸው ጉዳዮችና አድልዎ ይከሰታል!' ሶሐቦችም 'የአላህ መልክተኛ ሆይ! ምን ያዙናል?' አሉ። እርሳቸውም 'በናንተ ላይ ያለባችሁን ግዴታ ትወጣላችሁ። ለናንተ ያላችሁን ሐቅ ደግሞ ከአላህ ትጠይቃላችሁ።' አሉ።"

Sahih/Authentic. - [Al-Bukhari and Muslim]

ትንታኔ

ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) የሙስሊሞችን ገንዘብና ሌሎችንም አለማዊ ጉዳዮች በማዳላት ሙስሊሞችን በርሱ ላይ ካላቸው መብት በመከልከል እንደፈለጉ የሚያወጡ መሪዎች በሙስሊሞች ላይ እንደሚሾሙ ተናገሩ። በነርሱ ላይም የሚወገዙ ሃይማኖታዊ ጉዳዮች እንደሚኖራቸው ተናገሩ። ሶሐቦችም (ረዲየሏሁ ዐንሁም) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና በዚህ ሁኔታ ላይ ምን ማድረግ እንዳለባቸው ጠየቁ። ነቢዩም (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) በገንዘብ ጉዳይ ብቻቸውን መጠቀማቸው በናንተ ላይ ለነርሱ ልታሟሉ ግዴታ የሆነባችሁን ከመስማትና ከመታዘዝ እንዳይገታችሁ። ይልቁንም ታግሳችሁ መስማትና መታዘዝ ላይ አደራችሁን። በትእዛዞቻቸውም አትቃረኗቸው (አትከራከሯቸው)። እንዲያስተካክላቸው፣ ክፋታቸውንና ግፋቸውን እንዲከላከልላችሁ ለናንተ ያላችሁንም ሐቅ ከአላህ ጠይቁ!

ትርጉም: እንግሊዝኛ ፈረንሳይኛ ስፔንኛ ቱርክኛ የኡርዱ ቋንቋ ኢንዶኔዥያኛ ቦስንያኛ ሩስያኛ ባንጋሊኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ታጋሎግ ህንድኛ ቬትናማዊ ሲንሃላዊ ኡይጙራዊ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ማላያላምኛ ስዋሒልኛ ታሚልኛ ታይላንድኛ ቡሽትኛ አሳምኛ السويدية الهولندية الغوجاراتية الدرية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. ሐዲሡ የርሳቸውን ነቢይነት ከሚጠቁሙ ሐዲሶች መካከል አንዱ ነው። ይህም ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) በኡመታቸው ውስጥ የሚከሰተውን መናገራቸውና እንደተናገሩት ከመከሰቱ አንፃር ነው።
  2. ነፍሱን ዝግጁ እንዲያደርግና ባጋጠመው ወቅት ታጋሽና ምንዳውን የሚያስብ ሊሆን ዘንድ ለተፈተነ ሰው ለወደፊት ያጋጥመዋል ተብሎ የሚታሰብ መከራን ማሳወቅ እንደሚፈቀድ እንረዳለን።
  3. ከቁርአንና ሐዲሥ ጋር ያለ ትስስርን ማጠንከር ከፈተናና ልዩነት መውጫ መንገድ እንደሆነ እንረዳለን።
  4. ለመሪዎች በመልካም ጉዳይ መስማትና መታዘዝ ላይና ግፍ እንኳ ቢያደርሱ በነርሱ ላይ አምፆ ባለመውጣት ላይ መነሳሳቱን እንረዳለን።
  5. በፈተና ዘመን ሱናን መከተልና ጥበብን መጠቀም እንደሚገባ እንረዳለን።
  6. አንድ ሰው በርሱ ላይ ግፍ እንኳ ቢደርስበት ባለበት እውነት ላይ መቆም እንደሚገባው እንረዳለን።
  7. ይህ ሐዲሥ አንድ መርህን ይጠቁመናል። እርሱም፦ ከሁለት ክፋቶች ዝቅተኛውን ክፋት ይመረጣል፤ ወይም ከሁለት ጉዳቶች ቀላሉ ጉዳት ይመረጣል የሚል ነው።