عن مَعقِلِ بن يَسار المُزَنِيّ رضي الله عنه قال: إني سمعت رسول الله صلى الله عليه وسلم يقول:
«مَا مِنْ عَبْدٍ يَسْتَرْعِيهِ اللهُ رَعِيَّةً، يَمُوتُ يَوْمَ يَمُوتُ وَهُوَ غَاشٌّ لِرَعِيَّتِهِ، إِلَّا حَرَّمَ اللهُ عَلَيْهِ الْجَنَّةَ».

[صحيح] - [متفق عليه]
المزيــد ...

ከመዕቂል ቢን የሳር አልሙዘኒይ -አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸውና- እንደተላለፈው እንዲህ አሉ: እኔ የአላህን መልክተኛ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም እንዲህ ሲሉ ሰምቻቸዋለሁ:
"አላህ አንድ ሀላፊነት ላይ ሹሞት የተሰጠውን ሀላፊነት የሚያታልል ሆኖ የሚሞት ባሪያ የለም አላህ በርሱ ላይ ጀነትን እርም የሚያደርግ ቢሆን እንጂ።"

Sahih/Authentic. - [Al-Bukhari and Muslim]

ትንታኔ

እያንዳንዱ አላህ በሰዎች ላይ ተጠያቂና ሀላፊ ያደረገው ሁሉ እንደመሪነት ጠቅላይ ሀላፊነትን የሚያስተዳድርም ይሁን ወይም በቤቱ ሀላፊ እንደሆነ ወንድና በቤቷ ሀላፊ እንደሆነች ሴት ውስን ሀላፊነትም ይሁን የሀላፊነት ግዴታውን ካጓደለ፣ ቅን ሳይሆን ካጭበረበረና ዲናዊና ዓለማዊ ግዴታውን ካጠፋ ለከባድ ቅጣት እንደተገባ ነቢዩ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ተናገሩ።

ትርጉም: እንግሊዝኛ ፈረንሳይኛ ስፔንኛ ቱርክኛ የኡርዱ ቋንቋ ኢንዶኔዥያኛ ቦስንያኛ ሩስያኛ ባንጋሊኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ታጋሎግ ህንድኛ ቬትናማዊ ሲንሃላዊ ኡይጙራዊ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ማላያላምኛ ቴልጉ ስዋሒልኛ ታሚልኛ ቦርምኛ ታይላንድኛ ጀርመንኛ ጃፓንኛ ቡሽትኛ አሳምኛ አልባንኛ السويدية الهولندية الغوجاراتية الدرية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. ይህ ዛቻ በጠቅላይ መሪውና ሚኒስትሮቹ ላይ ብቻ የተገደበ ሳይሆን አላህ በሀላፊነት የሾመውን ሁሉ የሚያጠቃልል ነው።
  2. በአንዳች የሙስሊሞች ጉዳይ ላይ የተሾመ ሰው ያለበት ግዴታ ለነሱ ቅን መሆን፣ አደራውን በመወጣት ላይ መታገልና ማጭበርበርን መጠንቀቅ ነው።
  3. ጠቅላይም ይሁን ውስን፣ ትልቅም ይሁን ትንሽ ሀላፊነት ላይ የተሾመ ሁሉ ተጠያቂነቱ ትልቅ መሆኑን እንረዳለን።