+ -

عَنْ أَبِي ذَرٍّ رَضيَ اللهُ عنهُ قَالَ: قَالَ رَسُولُ اللهِ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ:
«يَا أَبَا ذَرٍّ إِذَا طَبَخْتَ مَرَقَةً فَأَكْثِرْ مَاءَهَا، وَتَعَاهَدْ جِيرَانَكَ».

[صحيح] - [رواه مسلم] - [صحيح مسلم: 2625]
المزيــد ...

ከአቡ ዘር ረዲየሏሁ ዐንሁ - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው እንዲህ አሉ: «የአላህ መልክተኛ ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና - እንዲህ ብለዋል:
"አቡ ዘር ሆይ! መረቅ የቀቀልክ ጊዜ ውሃውን አብዛ! ጎረቤቶችህንም ተከታተል።"»

[ሶሒሕ ነው።] - [ሙስሊም ዘግበውታል።] - [ሶሒሕ ሙስሊም - 2625]

ትንታኔ

ነቢዩ ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- አቡ ዘር አልጚፋሪይን ረዺየሏሁ ዐንሁ - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - መረቅ የቀቀለ ጊዜ ውሃውንና መረቁን እንዲያበዛና ከመረቁ ለጎረቤቶቹ በመላክም እንዲከታተላቸው አነሳሱት።

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. ከጎረቤት ጋር መልካም በሆነ መልኩ በመኗኗር ላይ መነሳሳቱን እንረዳለን።
  2. በጎረቤቶች መካከል ስጦታ መሰጣጠታቸው እንደሚወደድ እንረዳለን። ይህም ውዴታን ስለሚያመጣና ቅርርብን ስለሚጨምር ነው። ምግቡ የሚጣራ መአዛ ካለውና ጎረቤቶቹም እንደሚያስፈልጋቸው ከታወቀ ደግሞ ይህን ስጦታ መስጠት አፅንዖት የተሰጠው ጉዳይ ይሆናል።
  3. ብታንስ እንኳ የገራልንን ጥሩን ነገር በመለገስ ላይና ለሙስሊሞች ደስታ ምክንያት በመሆን ላይ መነሳሳቱን እንረዳለን።
ትርጉም: እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ ስፔንኛ ኢንዶኔዥያኛ ባንጋሊኛ ፈረንሳይኛ ቱርክኛ ሩስያኛ ቦስንያኛ ሲንሃላዊ ህንድኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ቬትናማዊ ታጋሎግ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ስዋሒልኛ ታይላንድኛ አሳምኛ الهولندية الغوجاراتية الدرية الرومانية المجرية الجورجية الخميرية الماراثية
ትርጉሞችን ይመልከቱ