عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ رَضيَ اللهُ عنهُ قَالَ: قَالَ رَسُولُ اللهِ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ:
«انْظُرُوا إِلَى مَنْ أَسْفَلَ مِنْكُمْ، وَلَا تَنْظُرُوا إِلَى مَنْ هُوَ فَوْقَكُمْ، فَهُوَ أَجْدَرُ أَلَّا تَزْدَرُوا نِعْمَةَ اللهِ عَلَيْكُمْ».

[صحيح] - [متفق عليه] - [صحيح مسلم: 2963]
المزيــد ...

ከአቡ ሁረይራ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው እንዲህ አሉ: «የአላህ መልክተኛ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን) እንዲህ ብለዋል:
"ከናንተ በታች ወዳለ ሰው ተመልከቱ እንጂ ከናንተ በላይ ወዳለ ሰው አትመልከቱ! ይህን ማድረጋችሁ (የበታቻችሁን ማየት) አላህ በናንተ ላይ የዋለውን ፀጋ አሳንሶ ከማየት ይታደጋችኃል።»

[ሶሒሕ ነው።] - [ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል።] - [ሶሒሕ ሙስሊም - 2963]

ማብራሪያ

ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና ሙስሊም የሆነ ሰው በዱንያ ጉዳዮቹ፣ በማዕረግ፣ በገንዘብ፣ በክብርና በሌሎችም ነገሮች በአንፃራዊ ሁኔታው ዝቅ ወዳለ ሰው እንዲመለከትና በዱንያዊ ጉዳዮች ደሞ ከርሱ የበላዩና በዱኒያ የሚበልጠው ወደሆነ ሰው እንዳይመለከት አዘዙ። ከርሱ በታች ወደሆነ ሰው መመልከት አላህ የዋለልህን ፀጋ እንዳታሳንስና ዝቅ እንዳታደርግ የሚያግዝ ነው።

ከሐዲሡ የሚቀሰሙ ቁምነገሮች

  1. መብቃቃት ከትላልቅ የአማኞች ስነምግባር መካከል አንዱ ነው። መብቃቃት በአላህ ውሳኔ የመውደድም ምልክት ነው።
  2. ኢብኑ ጀሪር እንዲህ ብለዋል: "ይህ ሐዲሥ የመልካም አይነቶችን ባጠቃላይ የሚሰበስብ ነው። ምክንያቱም የሰው ልጅ በዱንያ የሚበልጡትን የተመለከተ ጊዜ ነፍሱ እንደነርሱ አምሳያ መሆንን ትፈልጋለችና። እርሱ ዘንድ ያለውን የአላህን ፀጋም ያሳንሳል። የበለጡት ጋር ለመድረስ ወይም ለመቀራረብና ተጨማሪን ለማግኘትም ይጓጓል። ይህም አብዛኛው ሰዎች ላይ የሚስተዋል ነው። ነገር ግን በዱንያዊ ጉዳዮች የበታቾቹን የተመለከተ ጊዜ አላህ የዋለለትን ፀጋ በማስተዋል ያመሰግነዋልም ራሱንም ዝቅ ያደርጋል። በተሰጠው ፀጋም መልካሙን ይሰራበታል።"
ትርጉሞችን አሳይ
ቋንቋ: الإنجليزية الأوردية الإسبانية ተጨማሪ (43)
ተጨማሪ