عَنْ أَبِي حُمَيْدٍ السَّاعِدِيِّ رَضيَ اللهُ عنه قَالَ:
اسْتَعْمَلَ رَسُولُ اللَّهِ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ رَجُلًا عَلَى صَدَقَاتِ بَنِي سُلَيْمٍ، يُدْعَى ابْنَ اللُّتْبِيَّةِ، فَلَمَّا جَاءَ حَاسَبَهُ، قَالَ: هَذَا مَالُكُمْ وَهَذَا هَدِيَّةٌ. فَقَالَ رَسُولُ اللَّهِ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ: «فَهَلَّا جَلَسْتَ فِي بَيْتِ أَبِيكَ وَأُمِّكَ، حَتَّى تَأْتِيَكَ هَدِيَّتُكَ إِنْ كُنْتَ صَادِقًا» ثُمَّ خَطَبَنَا، فَحَمِدَ اللَّهَ وَأَثْنَى عَلَيْهِ، ثُمَّ قَالَ: «أَمَّا بَعْدُ، فَإِنِّي أَسْتَعْمِلُ الرَّجُلَ مِنْكُمْ عَلَى العَمَلِ مِمَّا وَلَّانِي اللَّهُ، فَيَأْتِي فَيَقُولُ: هَذَا مَالُكُمْ وَهَذَا هَدِيَّةٌ أُهْدِيَتْ لِي، أَفَلاَ جَلَسَ فِي بَيْتِ أَبِيهِ وَأُمِّهِ حَتَّى تَأْتِيَهُ هَدِيَّتُهُ، وَاللَّهِ لاَ يَأْخُذُ أَحَدٌ مِنْكُمْ شَيْئًا بِغَيْرِ حَقِّهِ إِلَّا لَقِيَ اللَّهَ يَحْمِلُهُ يَوْمَ القِيَامَةِ، فَلَأَعْرِفَنَّ أَحَدًا مِنْكُمْ لَقِيَ اللَّهَ يَحْمِلُ بَعِيرًا لَهُ رُغَاءٌ، أَوْ بَقَرَةً لَهَا خُوَارٌ، أَوْ شَاةً تَيْعَرُ» ثُمَّ رَفَعَ يَدَهُ حَتَّى رُئِيَ بَيَاضُ إِبْطِهِ، يَقُولُ: «اللَّهُمَّ هَلْ بَلَّغْتُ» بَصْرَ عَيْنِي وَسَمْعَ أُذُنِي.
[صحيح] - [متفق عليه] - [صحيح البخاري: 6979]
المزيــد ...
ከአቡ ሑመይድ አስሳዒዲይ -አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸውና- እንደተላለፈው እንዲህ ብለዋል:
«የአላህ መልክተኛ -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና - አንድ ኢብኑ ሉትቢየህ ተብሎ የሚጠራን ሰውዬ የበኒ ሱለይምን ጎሳ ዘካ እንዲሰበስብ ሾሙት፤ ሰብስቦ ሲመጣም ተሳሰቡት። እርሱም ሲያስረክብ እንዲህ አለ: "ይህ የናንተ ገንዘብ ነው። ይህ ደሞ የተሰጠኝ ስጦታ ነው።" የአላህም መልክተኛ -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና - እንዲህ አሉ: "እውነት ላንተ የተሰጠ ስጦታ ከሆነ ስጦታው ቤትህ እስኪመጣ ድረስ እናት አባትህ ቤት አትቀመጥም ነበር?" ቀጥለውም ኹጥባ አደረጉልን: አላህን ካመሰገኑና ካወደሱ በኋላም እንዲህ አሉ: "ከዚህ በመቀጠል እኔ አላህ በሰጠኝ ሹመት መሰረት ከናንተ መካከል አንድን ሰው ከሾምኩት በኃላ እኔ ዘንድ በመምጣት ይህ የናንተ ገንዘብ ነው። ይህ ደግሞ የተሰጠኝ ስጦታ ነው ይላል እንዴ?! ስጦታው ቤቱ እስኪመጣለት ድረስ እናት አባቱ ቤት አይቀመጥም ነበር? በአላህ እምላለሁ! ከናንተ መካከል አንዱ ያለአግባብ አንዳችን አይወስድም የትንሳኤ ቀን ተሸክሞት አላህን ቢገናኝ እንጂ ከናንተ መካከል አላህ ፊት የምትጮህ ግመል ወይም የምታጋሳ ከብት ወይም የምትጮህ በግ ተሸክሞ የሚቀርብን ሰው አውቃለሁ።" ቀጥለው "አላህ ሆይ መልዕክቴን አድርሻለሁን?" እያሉ የብብታቸው ንጣት እስኪታይ ድረስ እጃቸውን ከፍ አደረጉ። ይህንን ሁሉ አይኔም አይቷል ጆሮዬም ሰምቷል።»
[ሶሒሕ ነው።] - [ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል።] - [ሶሒሕ አልቡኻሪ - 6979]
ነቢዩ -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና - ኢበረኑ ሉትቢያህ የሚባልን ሰውዬ በኒ ሱለይም ከሚባል ጎሳ ዘካ እንዲሰበስብ ሾሙት። ወደ መዲና የተመለሰ ጊዜም ስለሰበሰበውና ስላወጣው ወጪ ተሳሰቡት። ኢብኑል ሉትቢያም እንዲህ አለ: ይህ የሰበሰብኩት የዘካ ገንዘባችሁ ነው። ይህ ደግሞ የተሰጠኝ ስጦታ ነው። ነቢዩም -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና - ለርሱ እንዲህ አሉት: እውነትህን ከሆነ ስጦታ እንደሚሰጥህ ለማየት እናት አባትህ ቤት አትቀመጥም ነበር? ላንተ ስጦታ እንዲሰጥህ ሰበብ የሆነክ የሰራህበት ስራ ይዞት የመጣው ሹመት ነው። ቤትህ ብትቀመጥ ኖሮ ለአንተ አንዳችም ስጦታ አይሰጥህም ነበር። ስጦታ በሚል ስም አንተ ጋር ስለደረሰ ብቻ ሐላል ልታደርገው አይገባም። ቀጥለውም ነቢዩ -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና - ተቆጥተው ኹጥባ ለማድረግ ወደ ሚንበር ወጡ። አላህን ካመሰገኑና ካወደሱም በኋላ እንዲህ አሉ: ከዚህ በመቀጠል: አላህ ለኔ እንድቆጣጠረው ባደረገኝ ዘካና ምርኮ ላይ ከናንተ መካከል አንድን ሰውዬ ሰራተኛ አደርገዋለሁ። ስራውን አጠናቆ ሲመጣ እንዲህ ይለኛልን!? ይህ ለናንተ ነው ይህ ደግሞ የተሰጠኝ ስጦታ ነው! ስጦታው ቤቱ እንድትመጣለት አባት እናቱ ቤት አይቀመጥም ነበርን!? በአላህ እምላለሁ! ከናንተ መካከል ማናችሁም የወሰደው የምትጮህ ግመል ወይም የምታጋሳ ከብት ወይም የምትጮህ በግ ብትሆን እንኳ የትንሳኤ ቀን ጫንቃው ላይ ተሸክሟት አላህን ቢገናኝ እንጂ ከሚሰጠው ሃላፊነት ያለአግባብ አንዳችን ወስዶ የሚቀር የለም። ዙሪያቸው የተቀመጡ ሰዎች የብብታቸውን ንጣት እስኪመለከቱ ድረስ እጃቸውን በጣም ከፍ አደረጉ። ቀጥለውም እንዲህ አሉ: "አላህ ሆይ! አድርሻለሁ፤ የአላህን ፍርድ ወደናንተ አድርሻለሁ።" ቀጥሎ አቡ ሑመይድ አስሳዒዲይ -አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸውና- ይህንን አይኑም ያየችው ጆሮውም የሰማው እንደሆነ ተናገረ።