عن أبي بَكرة رضي الله عنه قال: سمعت رسول الله صلى الله عليه وسلم يقول:
«إِذَا الْتَقَى الْمُسْلِمَانِ بِسَيْفَيْهِمَا فَالْقَاتِلُ وَالْمَقْتُولُ فِي النَّارِ»، فَقُلْتُ: يَا رَسُولَ اللهِ هَذَا الْقَاتِلُ، فَمَا بَالُ الْمَقْتُولِ؟ قَالَ: «إِنَّهُ كَانَ حَرِيصًا عَلَى قَتْلِ صَاحِبِهِ».

[صحيح] - [متفق عليه]
المزيــد ...

ከአቢ በክረህ -አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸው- እንደተላለፈው እንዲህ ብለዋል፦ የአላህን መልክተኛ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን እንዲህ ሲሉ ሰምቻዋለሁ፦
"ሁለት ሙስሊሞች በሰይፋቸው (ሊጋደሉ) የተገናኙ ጊዜ ገዳዩም ሆነ ተገዳዩ እሳት ውስጥ ናቸው። " እኔም "የአላህ መልክተኛ ሆይ! ይህ ገዳይ ሆኖ (እሳት መግባቱ መልካም) ተገዳዩ (እሳት የሚገባው) በምን ጥፋቱ ነው?" አልኩ። እርሳቸውም "እሱ ባልደረባውን ለመግደል ጉጉ ስለነበር ነው።" አሉ።

Sahih/Authentic. - [Al-Bukhari and Muslim]

ትንታኔ

ነቢዩ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን ሁለት ሙስሊሞች እርስ በርሳቸው እያንዳንዳቸው የባልደረባውን ህይወት ማጥፋትን ቋምጠው በሰይፋቸው ሊጋደሉ የተገናኙ እንደሆነ ሁለቱም እሳት እንደሚገቡ ተናገሩ። ገዳዩ ባለደረባውን በመግደሉ ምክንያት እሳት ውስጥ ይገባል። ሰሐቦች የተገዳዩ እሳት መግባት ግራ አጋባቸው: እንዴት የእሳት ይሆናል? ብለው ጠየቁ። ነቢዩም የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን ባልደረባውን ለመግደል በመጓጓቱ ፤ በገዳዩ ከመቀደም በስተቀር ከመግደል ምንም የከለከለው ነገር ስለሌለ እሱም ጭምር የእሳት መሆኑን ተናገሩ።

ትርጉም: እንግሊዝኛ ፈረንሳይኛ ስፔንኛ ቱርክኛ የኡርዱ ቋንቋ ኢንዶኔዥያኛ ቦስንያኛ ሩስያኛ ባንጋሊኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ታጋሎግ ህንድኛ ቬትናማዊ ሲንሃላዊ ኡይጙራዊ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ማላያላምኛ ቴልጉ ስዋሒልኛ ታሚልኛ ቦርምኛ ታይላንድኛ ጀርመንኛ ጃፓንኛ ቡሽትኛ አሳምኛ አልባንኛ السويدية الهولندية الغوجاراتية الدرية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. ወንጀል ለመስራት በልቡ የቆረጠና መዳረሻዎቹን የፈፀመ ሰው ለቅጣት የተገባ መሆኑን፤
  2. ሙስሊሞች እርስ በርስ በመጋደላቸው ዙሪያ ብርቱ ማስጠንቀቂያና የእሳት ዛቻም መምጣቱን፤
  3. በሙስሊሞች መካከል የተፈጠረው መጋደል በእውነት ጉዳይ ከሆነ ዛቻ ውስጥ አይካተትም። ለምሳሌ ከመሪ ትእዛዝ የወጡ ወሰን አላፊዎችና ሀገር የሚያበላሹን መዋጋትን ይመስል።
  4. ከባድ ወንጀል የሰራ ሰው በመስራቱ ብቻ ከሀዲ አይሆንም። ምክንያቱም ነቢዩ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን ሁለቱን እርስ በርስ የሚጋደሉትን ሙስሊሞች ብለው ጠርተዋቸዋልና።
  5. ሁለት ሙስሊሞች በማንኛውም ለመግደል የሚያደርስ በሆነ መሳሪያ ሊጋደሉ ተገናኝተው አንዱ አንዱን ቢገድል ገዳዩም ተገዳዩም እሳት ውስጥ ናቸው። ሐዲሡ ውስጥ ሰይፍ መጠቀሱ ለምሳሌ ያክል ብቻ ነው።