+ -

عَنْ مُعَاذِ بْنِ جَبَلٍ رضي الله عنه قَالَ:
كُنْتُ مَعَ النَّبِيِّ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ فِي سَفَرٍ، فَأَصْبَحْتُ يَوْمًا قَرِيبًا مِنْهُ وَنَحْنُ نَسِيرُ، فَقُلْتُ: يَا رَسُولَ اللهِ أَخْبِرْنِي بِعَمَلٍ يُدْخِلُنِي الجَنَّةَ وَيُبَاعِدُنِي عَنِ النَّارِ، قَالَ: «لَقَدْ سَأَلْتَنِي عَنْ عَظِيمٍ، وَإِنَّهُ لَيَسِيرٌ عَلَى مَنْ يَسَّرَهُ اللَّهُ عَلَيْهِ، تَعْبُدُ اللَّهَ وَلاَ تُشْرِكْ بِهِ شَيْئًا، وَتُقِيمُ الصَّلاَةَ، وَتُؤْتِي الزَّكَاةَ، وَتَصُومُ رَمَضَانَ، وَتَحُجُّ البَيْتَ» ثُمَّ قَالَ: «أَلاَ أَدُلُّكَ عَلَى أَبْوَابِ الخَيْرِ: الصَّوْمُ جُنَّةٌ، وَالصَّدَقَةُ تُطْفِئُ الخَطِيئَةَ كَمَا يُطْفِئُ الْمَاءُ النَّارَ، وَصَلاَةُ الرَّجُلِ مِنْ جَوْفِ اللَّيْلِ» قَالَ: ثُمَّ تَلاَ: «{تَتَجَافَى جُنُوبُهُمْ عَنِ الْمَضَاجِعِ}، حَتَّى بَلَغَ {يَعْمَلُونَ}» ثُمَّ قَالَ: «أَلاَ أُخْبِرُكَ بِرَأْسِ الأَمْرِ كُلِّهِ وَعَمُودِهِ، وَذِرْوَةِ سَنَامِهِ؟» قُلْتُ: بَلَى يَا رَسُولَ اللهِ، قَالَ: «رَأْسُ الأَمْرِ الإِسْلاَمُ، وَعَمُودُهُ الصَّلاَةُ، وَذِرْوَةُ سَنَامِهِ الجِهَادُ» ثُمَّ قَالَ: «أَلاَ أُخْبِرُكَ بِمَلاَكِ ذَلِكَ كُلِّهِ؟» قُلْتُ: بَلَى يَا نَبِيَّ اللهِ، فَأَخَذَ بِلِسَانِهِ قَالَ: «كُفَّ عَلَيْكَ هَذَا» فَقُلْتُ: يَا نَبِيَّ اللهِ، وَإِنَّا لَمُؤَاخَذُونَ بِمَا نَتَكَلَّمُ بِهِ؟ فَقَالَ: «ثَكِلَتْكَ أُمُّكَ يَا مُعَاذُ، وَهَلْ يَكُبُّ النَّاسَ فِي النَّارِ عَلَى وُجُوهِهِمْ أَوْ عَلَى مَنَاخِرِهِمْ إِلاَّ حَصَائِدُ أَلْسِنَتِهِمْ».

[صحيح بمجموع طرقه] - [رواه الترمذي وابن ماجه وأحمد] - [سنن الترمذي: 2616]
المزيــد ...

ከሙዓዝ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) -አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና- እንደተላለፈው እንዲህ አሉ :
«ከነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና ጋር ጉዞ ላይ ነበርኩ። አንድ እለት እየተጓዝን ሳለ ወደርሳቸው ቀረብኩኝና እንዲህ አልኳቸው: "የአላህ መልክተኛ ሆይ! ጀነት የሚያስገባኝና ከእሳትም የሚያርቀኝን ስራ ንገሩኝ?" እርሳቸውም " በርግጥም ስለ ትልቅ ጉዳይ ነው የጠየቅከኝ፤ ጉዳዩ አላህ በርሱ ላይ ላቀለለለት ሰው ቀላል ነው። አላህን ልትገዛና በርሱ ላይ ምንንም ላታጋራ፤ ሶላትን ቀጥ ልታደርግ (በአግባቡ ልትሰግድ)፤ ዘካን ልትሰጥ፤ ረመዳንን ልትጾም፤ የአላህንም ቤት ሐጅ ልታደርግ ነው።" አሉና ቀጥለውም እንዲህ አሉ: "የመልካም ነገሮችን በር አልጠቁምህምን? ጾም ጋሻ ነው፤ ውሃ እሳትን እንደሚያጠፋው ሁሉ ምፅዋትም ወንጀልን ታጠፋለች፤ የሰውዬው በሌሊቱ አጋማሽ የሚሰግደው ሶላት" አሉና ቀጥለው {ጎኖቻቸው ከመጋደሚያ ስፍራዎች ይራራቃሉ} ከሚለው {ይሰሩትም በነበሩት} እስከሚለው ድረስ [ሱረቱ ሰጅዳ: 16‐17] አነበቡ። ቀጥለውም "የነገሩ ሁሉ ራስ፣ ምሰሶውንና ሻኛውን ልንገርህን?" አሉ። እኔም "እንዴታ የአላህ መልክተኛ ሆይ!" አልኳቸው። እርሳቸውም "የነገሮች ሁሉ ራስ (ዋና) እስልምና ነው፤ ምሰሶው ሶላት ነው፤ ሻኛው ጂሃድ ነው።" አሉ። ቀጥለውም "ይህን ሁሉ የሚቆጣጠረውን ነገር ልንገርህን?" አሉ። እኔም "እንዴታ የአላህ ነቢይ ሆይ!" አልኳቸው። ምላሳቸውን ያዙና "በራስህ ላይ ይህቺን ቆጥባት!" አሉ። እኔም "የአላህ ነቢይ ሆይ! እኛ በምንናገረው እንያዛለንን?" አልኳቸው። እርሳቸውም "እናትህ ትጣህና ሙዓዝ ሆይ! ምላሳቸው ያጨደችው ካልሆነ በቀር ሰዎችን በፊታቸው ወይም በአፍጢማቸው እሳት ውስጥ የሚደፋቸው (ሌላ ነገር) አለ እንዴ?" አሉኝ።»

[ሶሒሕ ነው።] - [ኢብኑ ማጀህ ዘግበውታል። - ቲርሚዚ ዘግበውታል። - አሕመድ ዘግበውታል።] - [ሱነን ቲርሚዚ - 2616]

ትንታኔ

ሙዓዝ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንዲህ አሉ: ከነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ጋር ጉዞ ላይ ነበርኩ። አንድ እለት እየተጓዝን ሳለ ወደርሳቸው ቀረብ አልኩኝና እንዲህ አልኳቸው: የአላህ መልክተኛ ሆይ! ጀነት የሚያስገባኝና ከእሳትም የሚያርቀኝን ስራ ይንገሩኝ። እርሳቸውም እንዲህ አሉ: በነፍስ ላይ መስራቱ ከባድ ስለሆነ ስራ ነው የጠየቅከኝ። አላህ በርሱ ላይ ላቀለለለት ግን ገርና ቀላል ነው። የእስልምናን ግዴታዎች ፈፅም:
የመጀመሪያው: አላህን በብቸኝነት መገዛትና በርሱም አንዳችን አታጋራ፤
ሁለተኛው: በቀንና ምሽት አምስቱን ግዴታ ሶላቶች: ፈጅር፣ ዙህር፣ ዐስር፣ መጝሪብና ዒሻን መስፈርታቸውን፣ ማዕዘናቸውንና ግዴታዎቻቸውን አሟልተህ ቀጥ አድርገህ መስገድ ነው፤
ሶስተኛው: ግዴታ የሆነብህን ዘካ ማውጣት ነው: ይህም ገንዘብ በሸሪዓ የተገደበን መጠን በደረሰ ጊዜ ለሚገባው አካል የሚሰጥ በሁሉም ገንዘብ ላይ ግዴታ የሆነ ገንዘባዊ አምልኮ ነው፤
አራተኛው: ረመዳንን ትጾማለህ: እርሱም አምልኮን በመነየት ጎህ ከወጣችበት ወቅት ጀምሮ ፀሐይ እስክትገባ ድረስ ከመብላት፣ ከመጠጣትና ከሌሎችም የሚያስፈጥሩ ነገሮችም መቆጠብ ነው።
አምስተኛው: የሐጅ አምልኮን ለመተግበር አላህን ለማምለክ መካን በማሰብ የአላህን ቤት ሐጅ ማድረግ ነው።
ቀጥለውም ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) እንዲህ አሉ: ወደ መልካም በሮች የሚያደርስ መንገድ አላሳውቅህምን? ይህም እነዚህን ግዴታዎችና ሱና ተግባራትን በመከተል ነው:
የመጀመሪያው: ሱና ጾም መጾም ነው። ይህም ስሜትን በመስበርና ሀይልን በማድከም ወንጀል ላይ ከመውደቅ የሚከላከል ነው።
ሁለተኛው: ሰደቃ (ግዴታ ያልሆነ ምፅዋት) መስጠት ነው። ይህም ወንጀል ከተሰራ በኋላ ወንጀልን ታጠፋለች፣ ታስወግዳታለች፣ ፋናዋንም ታብሳታለች።
ሶስተኛው: በሌሊቱ የመጨረሻ ሲሶ የተሀጁድ ሶላት መስገድ ነው። ቀጥለው ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) {ጎኖቻቸው ከመጋደሚያ ስፍራዎች ይራራቃሉ} በሶላት፣ በዚክር፣ በመቅራትና በዱዓ {ጌታቸውን ይጠሩታል።} {ለመፍራትና ለመከጀል ከሰጠናቸውም (ጸጋ) ይለግሳሉ። ከዓይኖች መርጊያ ለእነርሱ የተደበቀላቸውን (ጸጋ) ማንኛይቱም ነፍስ አታውቅም።} ማለትም የትንሳኤ ቀን በጀነት ውስጥ በሚያገኙት ፀጋ አይኖቻቸው በርሱ የምትረጋበትን ነፍሳቸው አታውቅም። {ይሰሩትም በነበሩት ለመመንዳት።}
ቀጥለው ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና እንዲህ አሉ: የሃይማኖቱ መሰረት የሆነውን አልነግርህምን? መሰረቱ በርሱ ላይ የሚደገፍበት ምሰሶውንስ አልነግርህምን? ሻኛውንስ አልነግርህምን?
ሙዓዝም (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - "እንዴታ የአላህ መልክተኛ ሆይ!" አለ።
ነቢዩም (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና: የነገሮች ራስ (ዋና) እስልምና ነው። እርሱም ሁለቱ የምስክር ቃላቶች ናቸው። የሃይማኖቱ መሰረት ከሰውዬው ጋር የሚቆይለት በሁለቱ ቃላት ነው። ምሰሶው: ሶላት ነው። ቤት ያለምሰሶ እንደማይኖር ሁሉ ያለሶላትም እስልምና የለም። የሰገደ ሰው ሃይማኖቱ ይጠነክራልም ከፍ ይላልም። ሻኛውና ከፍታው ደሞ በጂሃድና የአላህን ቃል ከፍ ለማድረግ የእስልምና ጠላቶችን ለመዋጋት አቅምን በመለገስ ነው።
ቀጥለው ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና እንዲህ አሉ: ቀደም ብዬ የነገርኩህን ነገር የሚያስረውና የሚጠብቀውን ልንገርህን? ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና ምላሳቸውን ያዙና "ይህንን ቆጥብ። የማይመለከትህን አትናገር።" አሉት። ሙዓዝም: "ጌታችን በምንናገረው ሁሉ ይቀጣናል? ይተሳሰበናል? ይይዘናልን?"
ቀጥለውም ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና "እናትህ ትጣህ" አሉት። በዚህም እርሱን መርገም ፈልገው ሳይሆን ነገር ግን ዐረቦች ሊታወቅና ሊገነዘቡት የሚገባን ነገር ለማስገንዘብ የሚናገሩት ንግግር ነው። ቀጥለው እንዲህ አሉ "እንደክህደት፣ ዘለፋ፣ ስድብ፣ ሀሜት፣ ነገር ማሳበቅ፣ ቅጥፈትና በመሳሰሉት ምላሳቸው ባጨደችው ክፋት ካልሆነ በቀር ሰዎችን እሳት ውስጥ በፊታቸው የሚጥላቸውና የሚደፋቸው (ሌላ ነገር) አለ እንዴ?"

ትርጉም: እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ ስፔንኛ ኢንዶኔዥያኛ ፈረንሳይኛ ቱርክኛ ሩስያኛ ቦስንያኛ ሲንሃላዊ ህንድኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ቬትናማዊ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ስዋሒልኛ ቡሽትኛ አሳምኛ الهولندية الغوجاراتية Oromisht
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. ሶሐቦች (ረዺየሏሁ ዐንሁም) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - በእውቀት ላይ ያላቸውን ጥረት እንረዳለን። ለዛም ነቢዩን (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና በእውቀት ጉዳይ አብዝተው ይጠይቁ ነበር።
  2. ስራዎች ጀነት ለመግባት ምክንያት መሆኑን ማወቃቸው የሶሐቦች (ረዺየሏሁ ዐንሁም) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - ግንዛቤን ያስረዳናል።
  3. ከሙዐዝ (ረዺየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - የመጣው ጥያቄ በርግጥም ትልቅ ጥያቄ ነው። በእውነቱ ይህ ጥያቄ የህይወትና የመኖር ምስጢር ነውና። በዚህ አለም የሚገኝ የአደም ልጅና የጂን ፍጡር ሁሉ ፍፃሜው ወይ ጀነት ወይ እሳት ስለሆነ ይህ ጥያቄ እጅግ ትልቅ ጥያቄ ነው።
  4. ጀነት መግባት አምስቱን የእስልምና ማዕዘናት መፈፀምን ተከትሎ መሆኑን እንረዳለን። እነርሱም: ሁለቱ የምስክር ቃሎች፣ ሶላት፣ ዘካ፣ ፆምና ሐጅ ናቸው።
  5. የእስልምና መሰረት፣ ውዱ አላማና ትልቁ ግዴታ አላህን በአምልኮ ብቸኛ አድርጎ መነጠልና በርሱ ላይ አለማጋራት ነው።
  6. አላህ ለባሮቹ የምንዳና ወንጀል ማስማሪያ ሰበቦችን እንዲሰነቁ የመልካም በሮችን ለነርሱ መክፈቱ የርሱን እዝነት ያስረዳናል።
  7. ግዴታን ከተወጡ በኋላ በትርፍ ስራዎች ወደ አላህ የመቃረብን ትሩፋት እንረዳለን።
  8. ሶላት በእስልምና ያለው ደረጃ ድንኳን የሚቆምበት ምሰሶ ለድንኳኑ እንዳለው ደረጃ ያህል ነው። ምሰሶው ሲወድቅ ድንኳኑም እንደሚወድቀው ሁሉ ሶላት ስትወገድም እስልምናው አብሮ ይወገዳል።
  9. የሰው ልጅ ሃይማኖቱን ከሚጎዳው ነገር ምላሱን የመጠበቅ ግዴታ እንዳለበት እንረዳለን።
  10. ምላስን መቆጠብ፣ መጠበቅና መገደብ የመልካም ነገር ሁሉ መሰረት ነው።
ተጨማሪ