عن بعض أزواج النبي صلى الله عليه وسلم عن النبي صلى الله عليه وسلم قال:
«مَنْ أَتَى عَرَّافًا فَسَأَلَهُ عَنْ شَيْءٍ لَمْ تُقْبَلْ لَهُ صَلَاةٌ أَرْبَعِينَ لَيْلَةً».

[صحيح] - [رواه مسلم]
المزيــد ...

የነቢዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ባለቤት ከሆኑት መካከል ከአንዷ እንደተላለፈው ነቢዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም እንዲህ ብለዋል፦
"ሩቅ አዋቂ ነኝ ባይ ጋር የሄደና ስለአንዳች ነገር የጠየቀው የአርባ ሌሊት ሶላቱ ተቀባይነት አይኖራትም።"

Sahih/Authentic. - [Muslim]

ትንታኔ

ነቢዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ሩቅ አዋቂ ነኝ ባይ (ይህም ጠንቋይን፣ ኮኮብ እየተመለከቱ የሚተነብዩን፣ ጠጠርን ተንተርሰው የሚተነብዩንና የመሳሰሉትን የሩቅ እውቀትን ለመሞገት ለመነሻ ያህል የሚጠቀሙን የሚያጠቃልል የወል ስም ነው።) ጋር ከመሄድ አስጠነቀቁ። ሩቅ ከሆኑ ጉዳዮች መካከል አንዳችን መጠየቁ ብቻ በሱ ሳቢያ የአርባ ቀን የሶላቱን ምንዳ አላህ ይከለክለዋል። ይህም በዚህ ትልቅ ወንጀሉና ሀጢዐቱ ምክንያት መቀጣጫ እንዲሆነው ነው።

ትርጉም: እንግሊዝኛ ፈረንሳይኛ ስፔንኛ ቱርክኛ የኡርዱ ቋንቋ ኢንዶኔዥያኛ ቦስንያኛ ሩስያኛ ባንጋሊኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ህንድኛ ቬትናማዊ ሲንሃላዊ ኡይጙራዊ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ማላያላምኛ ቴልጉ ስዋሒልኛ ታሚልኛ ቦርምኛ ታይላንድኛ ጀርመንኛ ጃፓንኛ ቡሽትኛ አሳምኛ አልባንኛ السويدية الهولندية الغوجاراتية الدرية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. የጥንቆላ ክልክልነትን ፣ ወደጠንቋዮች መሄድና ስለሩቅ ሚስጥር መጠየቅም ክልክል መሆኑን እንረዳለን።
  2. ሰው ለወንጀሉ መቀጣጫ ይሆን ዘንድ የመልካም ስራውን ምንዳ ሊከለከል እንደሚችል እንረዳለን።
  3. አስትሮኖሚ (ዞዲያክ/ኮከብ ቆጠራ) በመባል የሚጠራው እውቀትና ወደርሱ መመልከት ፣ መዳፍና ሲኒን ለማወቅ ያህል ብቻ እንኳ ቢሆን ማንበብ እዚህ ሐዲሥ ውስጥ ይካተታል። ምክንያቱም ይህ ሁሉ ከጥንቆላና የሩቅ ምስጢር እውቀትን በመሞገት ውስጥ የሚመደብ ነውና።
  4. ሩቅ ሚስጥር አዋቂ ነኝ ባይ ጋር የሄደ ሰው ምንዳው ይህ ከሆነ ራሱ ሩቅ ሚስጥር አዋቂ ነኝ ባዩ ምንዳው ምን ይሆን?
  5. የአርባ ቀን ሶላቱ ስለምታብቃቃው ቀዳ የማውጣት ግዴታ አይኖርበትም። ነገር ግን በርሷ ምንም ምንዳ አያገኝም።