+ -

عَنِ ابْنِ عَبَّاسٍ رضيَ اللهُ عنهما:
أنَّهُ قَالَ لعَطَاءِ بْنِ أَبِي رَبَاحٍ: أَلَا أُرِيكَ امْرَأَةً مِنْ أَهْلِ الْجَنَّةِ؟ قُلْتُ: بَلَى، قَالَ: هَذِهِ الْمَرْأَةُ السَّوْدَاءُ، أَتَتِ النَّبِيَّ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ، قَالَتْ: إِنِّي أُصْرَعُ وَإِنِّي أَتَكَشَّفُ، فَادْعُ اللهَ لِي، قَالَ: «إِنْ شِئْتِ صَبَرْتِ وَلَكِ الْجَنَّةُ، وَإِنْ شِئْتِ دَعَوْتُ اللهَ أَنْ يُعَافِيَكِ» قَالَتْ: أَصْبِرُ، قَالَتْ: فَإِنِّي أَتَكَشَّفُ فَادْعُ اللهَ أَنْ لَا أَتَكَشَّفَ، فَدَعَا لَهَا.

[صحيح] - [متفق عليه] - [صحيح مسلم: 2576]
المزيــد ...

ከኢብኑ ዐባስ -አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው:
ኢብኑ ዓባስ ለዐጧእ ቢን አቢ ረባሕ እንዲህ አሉ:«ከጀነት ሰዎች መካከል የሆነች ሴት አላሳይህምን?" እኔም "እንዴታ!" አልኩኝ። እርሳቸውም እንዲህ አሉኝ: "ይህቺ ጥቁር ሴት ናት። ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በርሳቸው ላይ ይስፈንና) ዘንድ መጣችና እንዲህ አለች: ‹እኔ የሚጥል በሽታ አለብኝና እገላለጣለሁ። እንዲፈውሰኝ አላህን ለምኑልኝ።› እርሳቸውም: ‹ከፈለግሽ ታግሰሽ ላንቺ ጀነት አለሽ። ከፈለግሽ ደሞ ጤናን እንዲለግስሽ አላህን እለምንልሻለሁኝ።› አሏት። እርሷም ‹እታገሳለሁ።› ብላ እንዲህም አለች: ‹እኔ እገላለጣለሁኝ። እንዳልገላለጥ አላህን ለምኑልኝ።› እርሳቸውም ዱዓ አደረጉላት።"»

[ሶሒሕ ነው።] - [ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል።] - [ሶሒሕ ሙስሊም - 2576]

ትንታኔ

ኢብኑ ዐባስ (አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸውና) ለዐጧእ ቢን አቢረባሕ እንዲህ አሉ: "የጀነት ነዋሪ የሆነችን ሴት አላሳይህምን?" ዐጧእም "እንዴታ!" አለ። ኢብኑ ዐባስም እንዲህ አሉ: "ይህቺ ሐበሻዊት ጥቁር ሴት ናት። ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በርሳቸው ላይ ይስፈንና) ዘንድ መጣችና እንዲህ አለች: "የሚጥል በሽታ ስላለብኝ ይጥለኝና እገላለጣለሁኝ። ታዲያ እኔ ሳላውቀው ከሰውነቴ የተወሰነው ክፍል ይገለጣል። አላህ ጤናን እንዲለግሰኝ ለምኑልኝ።" እርሳቸውም እንዲህ አሏት: "ከፈለግሽ ታግሰሽ ላንቺ ጀነት አለልሽ። ከፈለግሽ ደግሞ አላህ ጤናን እንዲሰጥሽ እለምንልሻለሁኝ።" እርሷም እንዲህ አለች: "እንዲህ ከሆነ እታገሳለሁኝ። አክላም "ስወድቅ እንዳልገላለጥ ግን አላህን ይለምኑልኝ።" አለች። እርሳቸውም አላህን ለመኑላት።

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. በዱንያ በሚያጋጥሙ መከራዎች ላይ መታገስ ጀነትን ያስወርሳል።
  2. ነወዊይ እንዲህ ብለዋል: "ይህ ሐዲሥ የሚጥል በሽታ የተሟላን ምንዳ እንደሚያስመነዳ ይጠቁማል።"
  3. ሴት ሶሓቦች (አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸውና) የነበራቸውን ሀፍረትና ጥብቅነት እንዲሁም ለመሸፈን የነበራቸውን ጥረት እንረዳለን። ይህቺ ሴት አብዝታ ትፈራ የነበረው ጉዳይ ከሰውነቷ አንዳች አካል እንዳይገለጥባት ነበር።
  4. ኢብኑ ሐጀር እንዲህ ብለዋል: "ነፍሱ አቅም እንዳላት የተረዳና በጠንካራው ትእዛዝ ለመዘውተር ያልደከመ ሰው የተግራራውን ትእዛዝ ከመተግበር ይልቅ ጠንካራውን ትእዛዝ መተግበሩ ይበልጥለታል።"
  5. ኢብኑ ሐጀር እንዲህ ብለዋል: "ይህ ሐዲሥ በሽታዎችን ሁሉ በዱዓ፣ ወደ አላህ በመጠጋት ማከም በመድሓኒቶች ከመፈወስ የበለጠ ፈዋሽና ጠቃሚ እንደሆነ፣ የዱዓ ተፅእኖና የሚፈጥረው አካላዊ መነቃቃትም መድሃኒቶች ከሚፈጥሩት ተፅእኖ እጅግ የላቀ እንደሆነ እንረዳለን። ነገር ግን ይህ ስኬታማ የሚሆነው ሁለት ነገሮች ሲሟሉ ነው: የመጀመሪያው የሚፈለገው ከታማሚው ሲሆን እርሱም: በትክክል እድናለሁኝ የሚል ሃሳብ መሰነቅ ነው። ሁለተኛው: ከሚያክመው ሰው የሚፈለግ ሲሆን: ወደ አላህ የዞረበት ጥንካሬና ቀልቡ አላህን በመፍራትና በአላህ በመመካት የበረታ መሆኑ ነው።" አላህ የበለጠ አዋቂ ነው።
  6. ኢብኑ ሐጀር እንዲህ ብለዋል: "ይህ ሐዲሥ ህክምናን መተውም እንደሚፈቀድ ይጠቁማል።"
ትርጉም: እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ ስፔንኛ ኢንዶኔዥያኛ ባንጋሊኛ ፈረንሳይኛ ቱርክኛ ሩስያኛ ቦስንያኛ ሲንሃላዊ ህንድኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ቬትናማዊ ታጋሎግ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ስዋሒልኛ ታይላንድኛ አሳምኛ الدرية الرومانية المجرية الجورجية الخميرية الماراثية
ትርጉሞችን ይመልከቱ