عَنْ عَائِشَةَ أُمِّ المُؤمنينَ رضي الله عنها قَالَتْ:
دَخَلَ عَلَيَّ رَسُولُ اللهِ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ، وَقَدْ سَتَرْتُ سَهْوَةً لِي بِقِرَامٍ فِيهِ تَمَاثِيلُ، فَلَمَّا رَآهُ هَتَكَهُ وَتَلَوَّنَ وَجْهُهُ وَقَالَ: «يَا عَائِشَةُ، أَشَدُّ النَّاسِ عَذَابًا عِنْدَ اللهِ يَوْمَ الْقِيَامَةِ الَّذِينَ يُضَاهُونَ بِخَلْقِ اللهِ» قَالَتْ عَائِشَةُ: «فَقَطَعْنَاهُ فَجَعَلْنَا مِنْهُ وِسَادَةً أَوْ وِسَادَتَيْنِ».

[صحيح] - [متفق عليه]
المزيــد ...

ከአማኞች እናት ዓኢሻ (ረዲየሏሁ ዐንሃ) - አላህ መልካም ሥራዋን ይውደድላትና - እንደተላለፈው እንዲህ አለች:
"እቃ ክፍሌን (የተንቀሳቃሽ እንስሳ) ምስል ባለበት መጋረጃ ሸፍኜው ሳለ የአላህ መልክተኛ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) እኔ ዘንድ መጡ። የተመለከቱት ጊዜም ፊታቸው ተለዋውጦ ቀደዱትና እንዲህም አሉ 'ዓኢሻ ሆይ! የትንሳኤ ቀን አላህ ዘንድ ከሰዎች ሁሉ እጅግ ብርቱ ቅጣት የሚቀጡት እነዚያ በአላህ ፍጥረት የሚፎካከሩት ናቸው።'" ዓኢሻም እንዲህ አለች "ቆርጠነው በርሱ አንድ ትራስ ወይም ሁለት ትራስ አደረግንበት።"

Sahih/Authentic. - [Al-Bukhari and Muslim]

ትንታኔ

ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ቤታቸው ዓኢሻ (ረዲየሏሁ ዐንሃ) - አላህ መልካም ሥራዋን ይውደድላትና - ዘንድ ሲገቡ እቃ የምታስቀምጥበትን ትንሽዬ ክፍል ነፍስ ያላቸው ምስሎች ባለበት መጋረጃ ሸፍናው አገኟት። የፊታቸው ቀለምም ለአላህ ብለው በመቆጣታቸው ምክንያት ተለዋውጦ መጋረጃውን አወለቁት። እንዲህም አሉ: የትንሳኤ ቀን ከሰዎች ሁሉ እጅግ ብርቱ ቅጣት የሚቀጡት የአላህን ፍጥረት አስመስለው ምስል የሚያደርጉት ናቸው። ዓኢሻም እንዲህ አለች: እርሱን አንድ ትራስ ወይም ሁለት ትራስ አደረግነው።

ትርጉም: እንግሊዝኛ ፈረንሳይኛ ስፔንኛ ቱርክኛ የኡርዱ ቋንቋ ኢንዶኔዥያኛ ቦስንያኛ ሩስያኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ህንድኛ ቬትናማዊ ሲንሃላዊ ኡይጙራዊ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ማላያላምኛ ስዋሒልኛ ቡሽትኛ አሳምኛ السويدية الهولندية الغوجاراتية الدرية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. መጥፎን ነገር በማውገዛችን ሳቢያ የሚከሰት ትልቅ ብልሽት እስከሌለ ድረስ በተመለከትነው ቅፅበት ማውገዝ እንደሚገባና ማቆየትም እንደሌለብን እንረዳለን።
  2. የትንሳኤ ቀን ቅጣት እንደ ወንጀሉ ትልቀት ይበላለጣል።
  3. ነፍስ ያላቸው ነገሮችን ምስል ማድረግ ከትላልቅ ወንጀሎች መካከል አንዱ ነው።
  4. ምስል ማድረግ ከተከለከለባቸው ጥበቦች አንዱ ከአላህ አፈጣጠር ጋር መፎካከር ስለሆነ ነው። ይህም ምስል አድራጊው መፎካከር አሰበም አላሰበም እኩል ነው።
  5. ከጉዳዩ የተከለከለበትን ጎን ካራቅን በኋላም በርሱ መጠቀማችን ሸሪዓ ገንዘቦችን በመጠበቅ ላይ ያለውን ጉጉት ያስረዳናል።
  6. ነፍስ ያላቸውን ምስሎች በማንኛውም ቅርፅ ቢሆኑ እንኳ፣ ፕሮፌሽናል የሆነ ምስል ቢሆን እንኳ መፈብረክ ክልክል መሆኑን እንረዳለን።
ተጨማሪ