عَنِ ابْنِ عَبَّاسٍ رضي الله عنهما:
أَنَّ رَجُلًا أَتَى النَّبِيَّ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ، فَكَلَّمَهُ فِي بَعْضِ الْأَمْرِ، فَقَالَ: مَا شَاءَ اللهُ وَشِئْتَ، فَقَالَ النَّبِيُّ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ: «أَجَعَلْتَنِي لِلَّهِ عَدْلًا؟ قُلْ: مَا شَاءَ اللهُ وَحْدَهُ».

[إسناده حسن] - [رواه ابن ماجه والنسائي في الكبرى وأحمد]
المزيــد ...

ከኢብኑ ዓባስ (ረዲየሏሁ ዐንሁማ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው:
"አንድ ሰውዬ ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ዘንድ መጣና በሆኑ ጉዳዮች ዙሪያ አውርቷቸው 'የአላህና የእርሶ መሻት ሆነ።' አለ። ነቢዩም (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) 'ለአላህ ቢጤ አደረግከኝን? የብቸኛው አላህ መሻት ሆነ! በል!' አሉት።"

Its chain of narrators is Hasan/Sound. - [Ahmad]

ትንታኔ

አንድ ሰውዬ ወደ ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ዘንድ በመምጣት የግሉን ጉዳይ አወራቸውና ከዚያም "የአላህና የእርሶ መሻት ሆነ።" አላቸው። ነቢዩም (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ይህ ንግግሩን አወገዙት። የፍጡርን መሻት ከአላህ መሻት ጋር አቆራኝቶ መናገር ሙስሊም ሊለው የማይፈቀድለት ትንሹ ሺርክ መሆኑን ተናገሩ። ቀጥለውም ትክክለኛው አባባል "የብቸኛው አላህ መሻት ሆነ።" ማለቱ እንደሆነ ጠቆሙት። አላህን በመሻቱ መነጠል እንጂ በማንኛውም ማቆራኛ ቃላት የአንድንም አካል መሻት ከአሏህ ጋር ማቆራኘት የለበትም።

ትርጉም: እንግሊዝኛ ፈረንሳይኛ ስፔንኛ ቱርክኛ የኡርዱ ቋንቋ ኢንዶኔዥያኛ ቦስንያኛ ሩስያኛ ባንጋሊኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ታጋሎግ ህንድኛ ቬትናማዊ ሲንሃላዊ ኡይጙራዊ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ማላያላምኛ ስዋሒልኛ ቡሽትኛ አሳምኛ السويدية الهولندية الغوجاراتية الدرية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. "የአላህና የአንተ መሻት ሆነ።" ማለትና የመሳሰሉትን የባሪያን መሻት ከአላህ መሻት ጋር የሚያቆራኙ የቃላት አጠቃቀም ትንሹ ሺርክ በመሆኑ ክልክል ነው።
  2. መጥፎን ነገር ማውገዝ ግዴታ እንደሆነ እንረዳለን።
  3. የአላህ መልክተኛ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) የተውሒድን ድንበር ጠብቀዋል። የሺርክን መንገዶችንም ዘግተዋል።
  4. ነቢዩን (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) በመከተል መጥፎን በምናወግዝ ወቅት ለሚመከረው አካል የተፈቀደን ተለዋጭ መጠቆሙ የተሻለ ነው።
  5. በዚህ ሐዲሥ ውስጥ ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) "የብቸኛው አላህ መሻት ሆነ።" ማለትን በከለከሉበት በዚሁ ሐዲሥና በሌላ ሐዲሥ ደግሞ "የአላህ መሻት ሆነ ከዚያም የአንተ መሻት ሆነ። በል!" በማለታቸው መካከል የሚስማማው "የአላህ መሻት ሆነ ከዚያም የአንተ መሻት ሆነ።" ማለት የሚፈቀድ ሲሆን "የብቸኛው አላህ መሻት ሆነ።" ማለት ደግሞ በላጩ ነው በሚል ነው።
  6. "የአላህ መሻት ሆነ ከዚያም የአንተ መሻት ሆነ።" ማለትህ የሚፈቀድ ሲሆን ነገር ግን በላጩ "የብቸኛው አላህ መሻት ሆነ።" ማለት ነው።