عن أنس بن مالك رضي الله عنه:
أَنَّ النَّبِيَّ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ وَمُعَاذٌ رَدِيفُهُ عَلَى الرَّحْلِ قَالَ: «يَا مُعَاذُ بْنَ جَبَلٍ»، قَالَ: لَبَّيْكَ يَا رَسُولَ اللهِ وَسَعْدَيْكَ، قَالَ: «يَا مُعَاذُ»، قَالَ: لَبَّيْكَ يَا رَسُولَ اللهِ وَسَعْدَيْكَ، ثَلَاثًا، قَالَ: «مَا مِنْ أَحَدٍ يَشْهَدُ أَنْ لَا إِلَهَ إِلَّا اللهُ وَأَنَّ مُحَمَّدًا رَسُولُ اللهِ صِدْقًا مِنْ قَلْبِهِ إِلَّا حَرَّمَهُ اللهُ عَلَى النَّارِ»، قَالَ: يَا رَسُولَ اللهِ، أَفَلَا أُخْبِرُ بِهِ النَّاسَ فَيَسْتَبْشِرُوا؟ قَالَ: «إِذًا يَتَّكِلُوا». وَأَخْبَرَ بِهَا مُعَاذٌ عِنْدَ مَوْتِهِ تَأَثُّمًا.

[صحيح] - [متفق عليه]
المزيــد ...

ከአነስ ቢን ማሊክ -አላህ መልካም ስራውን ይውደድለትና- እንደተላለፈው:
"ነቢዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ግመል ላይ ሆነው ሙዓዝ ከኃላ ተፈናጦ ሳለ እንዲህ አሉ: 'አንተ ሙዓዝ ቢን ጀበል ሆይ' እርሱም ሶስቴ 'አቤት ብያለው በደስታ የአላህ መልክተኛ ሆይ!' አሁንም 'ሙዓዝ ሆይ!' አሉት: እሱም 'አቤት ብያለው በደስታ የአላህ መልክተኛ ሆይ!' አለ። ሶስት ጊዜ ደገሙትና ቀጥለውም ' አላህ በእርሱ ላይ እሳትን እርም ቢያደርግ እንጂ አንድም በእውነተኛ ልቡ ከአላህ በስተቀር በእውነት የሚመለክ አምላክ እንደሌለ ሙሐመድም የአላህ መልክተኛ መሆናቸውን የሚመሰክር የለም።' አሉ። እርሱም 'የአላህ መልክተኛ ሆይ! ይህንን ለሰዎች ነገሬ ላበስራቸው እንዴ?' አለ። እሳቸውም 'ከነገርካቸውማ (በዚህ ሐዲሥ ላይ) ይደገፋሉ (ይሰንፋሉ)።' አሉ። ሙዓዝ ይህንን ሐዲስ የተናገረው ወንጀል ውስጥ ላለ መውደቅ ብሎ ሊሞት ሲል ነው።"

Sahih/Authentic. - [Al-Bukhari and Muslim]

ትንታኔ

ሙዓዝ ቢን ጀበል -አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸውና- ከነቢዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም መጋጓዣ ኋላ ተፈናጦ ሳለ እሳቸው "ሙዓዝ ሆይ!" በማለት ጠሩት። ለርሱ የሚነግሩት ነገር አንገብጋቢ መሆኑን አፅንኦት ለመስጠትም ጥሪያቸውን ሶስት ጊዜ ደጋገሙት።
ሙዓዝም -አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸውና- በነዚህ ጥሪዎች ሁሉ "ለበይከ ያረሱለሏህ ወሰዕደይክ" ማለትም የአላህ መልክተኛ ሆይ!ደጋግሜ በደስታ አቤት ብያለሁ። እያለ ይመልስ ነበር።
ነቢዩም ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ከአላህ በስተቀር በእውነት የሚመለክ እንደሌለና ሙሐመድም የአላህ መልክተኛ መሆናቸውን ሳይዋሽ በእውነተኛ ልቡ የሚመሰክር ሆኖ በዚህ ሁኔታው ላይ ከሞተ አላህ እሳትን በርሱ ላይ እርም እንደሚያደርግ ነገሩት።
ሙዓዝም -አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸውና- ሰዎች እንዲደሰቱና በመልካም እንዲበሰሩ ልንገራቸውን? በማለት ነቢዩን ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ጠየቀ።
ነቢዩም ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም በዚህች ንግግር ላይ በመደገፍ ስራዎቻቸው እንዳታንስ ፈሩ።
ሙዓዝም እውቀትን የመሸሸግ ወንጀል ውስጥ መውደቅን በመፍራት ከመሞታቸው በፊት ካልሆነ በቀር ከዛ በፊት ይህችን ሐዲሥ ለአንድም አልተናገረም።

ትርጉም: እንግሊዝኛ ፈረንሳይኛ ስፔንኛ ቱርክኛ የኡርዱ ቋንቋ ኢንዶኔዥያኛ ቦስንያኛ ሩስያኛ ባንጋሊኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ታጋሎግ ህንድኛ ቬትናማዊ ሲንሃላዊ ኡይጙራዊ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ማላያላምኛ ቴልጉ ስዋሒልኛ ታሚልኛ ቦርምኛ ታይላንድኛ ጃፓንኛ ቡሽትኛ አሳምኛ አልባንኛ السويدية الهولندية الغوجاراتية الدرية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. ነቢዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ሙዓዝን ከመጓጓዣ እንስሳቸው ኋላ ማፈናጠጣቸው የሳቸውን መተናነስ ያስረዳናል።
  2. ሙዓዝ እሳቸው ለሚናገሩት ንግግር ንቃቱ እንዲበረታ ሙዓዝን ደጋግመው መጥራታቸው የነቢዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለምን የማስተማር ስልት እንረዳለን።
  3. "ላኢላሃ ኢለሏህ እና ሙሐመድ ረሱሉሏህ" የሚሉት የምስክርነት ቃላት ካላቸው መስፈርቶች መካከል ተናጋሪው ሳይዋሽ ወይም ሳይጠራጠር እውነተኛና እርግጠኛ መሆኑ አንዱ ነው።
  4. የተውሒድ ሰዎች በጀሀነም እሳት ውስጥ አይዘወትሩም። በወንጀሎቻቸው አማካኝነት ቢገቡ እንኳ ከፀዱ በኋላ ከርሷ ይወጣሉ።
  5. ሁለቱ የምስክርነት ቃላቶችን በእውነት ለተናገረ ሰው ያላቸውን ትሩፋት እንረዳለን።
  6. ሐዲሥን በመናገር ተከትሎ የሚመጣ ችግር (መፍሰዳህ) ካለ አንዳንድ ጊዜ ሐዲሡን ከመናገር መቆጠብ እንደሚፈቀድ እንረዳለን።