عَنْ أَبِي سَعِيدٍ الْخُدْرِيِّ وَعَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ رضي الله عنهما عَنِ النَّبِيِّ صلى الله عليه وسلم قَالَ:
«مَا يُصِيبُ الْمُسْلِمَ مِنْ نَصَبٍ وَلَا وَصَبٍ وَلَا هَمٍّ وَلَا حُزْنٍ وَلَا أَذًى وَلَا غَمٍّ حَتَّى الشَّوْكَةِ يُشَاكُهَا إِلَّا كَفَّرَ اللهُ بِهَا مِنْ خَطَايَاهُ».

[صحيح] - [متفق عليه]
المزيــد ...

ከአቡ ሰዒድና አቡ ሁረይራህ (ረዲየሏሁ ዐንሁማ) -አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸውና- እንደተላለፈው ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) እንዲህ ብለዋል፦
"አላህ በሷ ምክንያት ከወንጀሎቹ የሚምርለት ቢሆን እንጂ አንድን ሙስሊም ድካም፣ በሽታ፣ ሀሳብ፣ ሀዘን፣ ጉዳት፣ ጭንቀት የምትወጋው አንዲት እሾክ እንኳ (በከንቱ) አታገኘውም።"

Sahih/Authentic. - [Al-Bukhari and Muslim]

ትንታኔ

ሙስሊምን ከበሽታዎች ፣ ከጭንቀቶች፣ ከሀዘኖች፣ ከችግሮች፣ ከመከራዎች፣ ከመአቶች እንዲሁም ከፍርሀትና ረሀብ ቢደርስበት አንዲት እሾህ እንኳ ብትወጋውና ብታሳምመው ለርሱ ወንጀሎቹን ማስማሪያና ኃጢአቶቹን ማስሰረያ እንደሚሆንለት የአላህ መልክተኛ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ገለፁ።

ትርጉም: እንግሊዝኛ ፈረንሳይኛ ስፔንኛ ቱርክኛ የኡርዱ ቋንቋ ኢንዶኔዥያኛ ቦስንያኛ ሩስያኛ ባንጋሊኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ታጋሎግ ህንድኛ ቬትናማዊ ሲንሃላዊ ኡይጙራዊ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ማላያላምኛ ቴልጉ ስዋሒልኛ ታሚልኛ ቦርምኛ ታይላንድኛ ጀርመንኛ ጃፓንኛ ቡሽትኛ አሳምኛ አልባንኛ السويدية الهولندية الغوجاراتية الدرية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. አላህ በአማኝ ባሮቹ ላይ በሚደርስባቸው ትንሽ ጉዳት ምክንያት ወንጀሎችን መማሩ በአማኝ ባሮቹ ላይ ያለው ችሮታና እዝነቱን ይገልፃል።
  2. አንድ ሙስሊም የሚደርስበት ችግር ለደረጃው ከፍታና ለወንጀሉ መማሪያ እንዲሆንለት አላህ ዘንድ የሚያገኘውን ምንዳ በማሰብ፤ በትንሹም ሆነ በትልቁ መከራ ሁሉ ሊታገስ ይገባዋል።